🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምራ የምታጠናቅቅ ሀገር ሆናለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፕሮጀክት ግንባታ ዙሪያ ማብራሪያቸው፤ መንግስት የጀመራቸው አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች ተከታታይ ዕድገት ማስገኘታቸውን አስታውቀዋል።
በማሻሻያው ድጋፍ በዚህ ዓመት ብቻ በርካታ ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች ተገንብተው መጠናቀቃቸውን አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሰባት የሀገር ውስጥ ኤርፖርቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን እና ሌሎችም በርካታ የልማት ፕሮጀክቶች በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አስረድተዋል።
ለአብነትም በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ከ1 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የአስፓልት መንገድ መገንባቱ ጠቅሰዋል።
መንግሥት ለረጅም ዓመታት ሳይጠናቀቁ የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ረገድ በልዩ ትኩረትና ክትትል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይም የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች ከዳር የማድረስና አዳዲሶቹን በሂደት የመተግበር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው አቅም በፈቀደ መጠን የሕዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች በትጋት እንደሚከናወኑ አረጋግጠዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026