የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በማነቃቃትና በመደገፍ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያሳዩ ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በማነቃቃትና በመደገፍ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያሳዩ መሆኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ሙሐመድ ኢብራሂም ገለጹ።

ኢትዮጵያ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት የሀገሪቱን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማረጋገጥና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ እየሰራች ትገኛለች።

ከእነዚህም መካከል በታዳሽ ኃይል ማመንጫ፣ በታላላቅ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶች፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲሁም በከተማ ውበትና በኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ሰፊ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ እየተገነቡ ይገኛሉ።

እነዚህ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በሚገነቡበት ወቅት በርካታ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር፣ የሀገር ውስጥ ምርታማነትን በማሳደግና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ የጎላ ሚና እንዳላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ ይገልጻሉ።

ትናንት በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን ጀምራ በማጠናቀቅ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት በአሁኑ ወቅት የጀመራቸውን ሜጋ ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የፕሮጀክቶቹ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ፋይዳ በምሁራንና በባለሙያዎች ዘንድ ሰፊ ትኩረት እየተሰጠው ይገኛል።

ፕሮጀክቶቹ የሕዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያሻሽሉ እና የኢትዮጵያን ጀምሮ የመጨረስ አቅም በይፋ የሚያረጋግጡ እንደሆኑ አንስተዋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ሙሐመድ ኢብራሂም እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በብዝሃ ዘርፍ ላይ ያተኮረ መሆኑ በሁሉም ዘርፎች ተመጣጣኝ የሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ አግዟል።

በተለይም ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የሚያመነጩት ገቢ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በመደገፍ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያሳዩ እንደሆነ ጠቁመው፤ ይህም የሀገሪቷን ገቢ እና ወጪን በማስተካከል ጤናማ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል።

ይህም የሀገሪቷ ዓመታዊ በጀት በየጊዜው ጭማሪ እንዲያሳይ እንዲሁም ፕሮጀክቶችን የመፈጸም አቅም እንዲያድግ አይነተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ እና በአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፎች ያከናወነቻቸው የሪፎርም ተግባራት ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የኢኮኖሚ ባለቤት እንደሚያደርጋትም ትልቅ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ "ብሪክስን" ጨምሮ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የጀመረችው የንግድ ግንኙነት እና የወጪ ንግድ መጨመር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ እንደሆነም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026