የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ለዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ስኬት የመንግስትን ቀጣይነት ያለው ቁርጠኝነት ያረጋገጠ ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትላንትናው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰጡት ማብራሪያ ለዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ስኬት የመንግስትን ቀጣይነት ያለው ትጋትና ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን በአፋር ክልል የሰመራ ሎጊያ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸው ይታወቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸውም መንግስት በተለይም ለዘላቂ ሰላም፣ ለንግግርና ውይይት ሁልጊዜም ዝግጁ መሆኑን አስረድተዋል።

የግጭትና ጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያስፈልገን ሰላም፣ ትብብር እና አብሮነት ነው ብለዋል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ በአፋር ክልል ሰመራ ሎጊያ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ለዘላቂ ሰላምና የልማት ስራዎች ስኬት የመንግስትን ቀጣይነት ያለው ትጋትና ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል አቶ ዋሲሁን አያሌው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤት ተገኝተው የሰጡት ማብራሪያ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን የዳሰሰ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም የሰላም ጉዳይ ወሳኝ መሆኑን በማንሳት የግጭትና ጦርነት እሳቤ አውዳሚና ትርፍ የሌለው በመሆኑ የሰላም ጥረታችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸው መንግስት ለሰላም ያለውን ጽኑ አቋም ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ የትኛውንም ችግር በውይይትና በንግግር መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት የሰጠ በመሆኑ ሁላችንም የሰላምን ጉዳይ የራሳችን አጀንዳ አድርገን መስራት አለብን ነው ያሉት።

ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ ወጣት ሙሳ መሐመድ በበኩሉ፥ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁላችንንም ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ የልማት ሥራዎች ተሰርተዋል ይህንንም በበቂ ማሳያዎች መግለጽ ይቻላል ብሏል።

በመሆኑም በልማት የተገኘውን ስኬት በሰላም ግንባታም በመድገም ለሁለንተናዊ እድገትና የጋራ ተጠቃሚነት መስራት ይገባናል ሲል ገልጿል።

አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ በማድረግ፣ በከተሞች አካባቢ ቀልጣፋ የአገልግሎት ተጠቃሚነትን በፍጥነት ማሳደግ መቻሉን የገለጹት ደግሞ አቶ ረምዚ ይማም ናቸው።

የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድም አሁን ባለው ሁኔታ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሞዴል ትምህርት ቤቶች መገንባታቸን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚገባ መግለጻቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026