የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫን በመከተልና በተደመረ አቅም በማልማት ባለፉት አምስት አመታት የተመዘገበው ስኬት የሚደነቅ ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረማያ፤ ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የብዝሃ ኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫን በመከተል አቅምን አካብቶ በተደመረ አቅም በማልማት ባለፉት አምስት አመታት የተመዘገበው ስኬት የሚደነቅ መሆኑን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና የአግሪካልቸራል ኢኮኖሚክስ ምሁር የሆኑት ከዲር ጀማል (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁሉም ክልሎች በግብርና፣ ቱሪዝም፣ በመሠረተ-ልማትና በማህበራዊ ዘርፎች በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም የወጪ ንግድ ገቢ 11 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን፤ በተለይም ከወርቅ 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር እና ከቡና 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን አብራርተዋል።

ኢዜአ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራሪያ ተከትሎ ያነጋገራቸው በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲንና የአግሪካልቸራል ኢኮኖሚክስ ባለሙያ ከዲር ጀማል (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ማብራርያ ስለመከታተላቸው ተናግረዋል።

በተለይም ሀገሪቱ ግብርናን በማስፋትና በማዘመን ከሚከናወነው ስራ በተጨማሪ በኢንዱስትሪና በሌሎች የሚከናወኑት ተግባራት አበረታች ውጤቶች ስለመመዝገባቸው ማንሳታቸውን ገልጸዋል።

ከለውጡ ማግስት በግብርናው ዘርፍ መሰረቱን በማስፋት የተከናወኑት ተግባራት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ እድገት፣ በስራ እድል ፈጠራና ድህነትን በመቀነስ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

እንደ ዶክተር ከዲር ገለጻ፤ ቀደም ሲል ሀገሪቱ ካልተጠቀመችባቸው ዘርፎች መካከል ቱሪዝም መሆኑን በመጥቀስ ከለውጡ ወዲህ ትኩረት ተሰጥቶ የተከናወነውና ለውጥ የተመዘገበበት ዘርፉ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት በከተሞች የተገነቡት የኮሪደር ልማት ሰራዎች ቅርሶችን ከማደስና ከመጠበቅ ባሻገር በርካታ ሎጅ ተገንብተዋል፣ ሆቴሎች ተስፋፍተዋል፤ በዚህም የጎብኚው ቁጥር በመጨመር በዘርፉ የሚገኘው ገቢ እያጎለበተ ይገኛል ብለዋል።

ከመሰረተ ልማት ጋር በተያያዘም በኮሪደር ልማትና በሌሎች ኢኮኖሚውን አቅምና ፍሰት የሚያጎለብቱና መስተጋብሮችን በቀላሉ የሚያሳልጡ በርካታ ልማቶች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በዲጂታል መሰረተ ልማትም የተከናወኑ ተግባራት ኢትዮዽያን ወደ ተሟላ ዲጂታላይዜሽን ያሸጋገሩ ተግባራት ስለመከናወናቸው አንስተዋል።

ከለውጡ በፊት 2 ቢሊዮን ዶላር የነበረው ዓመታዊ የውጪ ንግድ ገቢ ባለፉት ዓመታት በተከናወነው ስራ ወደ 11 ቢሊዮን ዶላር ማደጉ መንግስት ምን ያህል የኢኮኖሚ መሰረቱን እንዳሰፋ የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026