የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአሪ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ5 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ይጠበቃል

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት መታቀዱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የአሪ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የዞኑ ሥነ-ምህዳር ለእርሻ ሥራው ተስማሚ በመሆኑ በተለይ በደጋው አካባቢ ዓመቱን ሙሉ ዝናብ ለማግኘት ያስችላል።

በቆላማ አካባቢዎች ደግሞ የተለያዩ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም የእርሻ ሥራው እንደሚከናወን ተናግረዋል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻም ከ46 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።

በዚህም በደጋማው የዞኑ አካባቢ ገብስ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ባቄላ እና አተር በስፋት እንደሚመረት ጠቅሰው፤ በቆላማ አካባቢዎች ደግሞ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ለውዝ፣ ሰሊጥ፣ ማሾ፣ ጤፍ እና ሱፍ በስፋት እየለማ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

አርሶ አደሩ ኮረሪማ፣ ቡና፣ ዝንጅብል፣ ሱፍ፣ ካሳቫ እና ሌሎች በገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ ምርቶችን በስፋት በማልማት ተጠቃሚ እንዲሆንም በትኩረት እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል።

ለእርሻ ሥራው ስኬታማነት በዩኒየኖች አማካኝነት ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እየቀረበ መሆኑንም አክለዋል።

በዞኑ የደቡብ አሪ ወረዳ አርሶ አደር ማርቆስ አንክሺ ጥሩ ምርት ያገኙበትን የበልግ ሰብል በማንሳት፣ በአሁኑ ወቅት ማሳቸውን ለመኸር እርሻ እያዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።

አስፈላጊውን ግብዓት ተጠቅመው ማሳቸውን እንደሚያለሙና የተሻለ ምርት ለማግኘት እንደሚሠሩም አርሶ አደሩ ተናግረዋል።

ሌላው የወረዳው አርሶ አደር አቶ አዲሱ ፈለቀ በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የመኸር እርሻ የተሻለ ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

የግብርና ባለሙያዎችም እገዛ እያደረጉላቸው መሆኑን ጠቅሰው፣ የምርጥ ዘርና ማዳበሪያ አቅርቦቱ በወቅቱ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በዘንድሮው የመኸር አዝመራ በቆሎ በስፋት እንደሚያለሙ የጠቆሙት አቶ አዲሱ፤ በተጨማሪም አትክልቶችን በማልማት ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026