የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአዲስ አበባ ከተማ ዓመታዊ ገቢ የመሰብሰብ አቅም 350 ቢሊዮን ብር ደርሷል-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን ገቢ አሰባሰብ በማዘመን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዓመታዊ የገቢ የመሰብሰብ አቅም 350 ቢሊዮን ብር ገቢ ማድረስ እንደተቻለ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉባኤው ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ነው።

በገቢ አሰባሰብ ሪፖርታቸው፤ መዲናዋ ከአፍሪካ ስድስት ታላላቅ ከተሞች ጋር በተደረገ ዝርዝር ጥናት፣ በበጀት አጠቃቀምና ለዘላቂ ልማት በማዋል ረገድ ቀዳሚ ሆና መመረጧን ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት በ2013 በጀት ዓመት 51 ቢሊዮን ብር የነበረው የከተማዋ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት ወደ 350 ቢሊዮን ብር ማደጉን አስታውቀዋል።

በበጀት ዓመቱም ለመሰብሰብ በዕቅድ የተያዘውን ግብ 100 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ አስረድተዋል።

የዘንድሮው የገቢ አሰባሰብ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ116 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ብልጫ እና የ50 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን በሪፖርቱ አመላክተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ የገቢ አቅሙን ለማሳደግም የፍትሐዊነት መርህን በተከተለ መልኩ እንዲሰበሰብ በሰፊው መሠራቱን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026