🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባን ገቢ አሰባሰብ በማዘመን የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዓመታዊ የገቢ የመሰብሰብ አቅም 350 ቢሊዮን ብር ገቢ ማድረስ እንደተቻለ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉባኤው ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ነው።
በገቢ አሰባሰብ ሪፖርታቸው፤ መዲናዋ ከአፍሪካ ስድስት ታላላቅ ከተሞች ጋር በተደረገ ዝርዝር ጥናት፣ በበጀት አጠቃቀምና ለዘላቂ ልማት በማዋል ረገድ ቀዳሚ ሆና መመረጧን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት በ2013 በጀት ዓመት 51 ቢሊዮን ብር የነበረው የከተማዋ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት ወደ 350 ቢሊዮን ብር ማደጉን አስታውቀዋል።
በበጀት ዓመቱም ለመሰብሰብ በዕቅድ የተያዘውን ግብ 100 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ አስረድተዋል።
የዘንድሮው የገቢ አሰባሰብ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ116 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ብልጫ እና የ50 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን በሪፖርቱ አመላክተዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የገቢ አቅሙን ለማሳደግም የፍትሐዊነት መርህን በተከተለ መልኩ እንዲሰበሰብ በሰፊው መሠራቱን አስረድተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026