የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ የዲጂታል እመርታ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማሳለጥ ውጤታማነት እያሳደገ ነው

Jul 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል እመርታ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማሳለጥ ውጤታማነት እያሳደገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ30ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፣ በሀገሪቱ በትምህርት ዘርፍ የተመዘገበው ስኬት እጅግ የሚያኮራ እና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸዋል።

መንግሥት ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ ለጥራት፣ ለቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የፈተና ስርቆትን ለመከላከል የሰጠው ትኩረት ዘርፉን በአዲስ ምዕራፍ ላይ ለማስቀመጥ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

ይህ የተቀናጀ ጥረት የትምህርት ጥራትን አስተማማኝ መሰረት ላይ ለመጣልና የትውልዱን ብቃት ለማሳደግ በሚደረገው ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ መንግሥት በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ስብራቶችን ለመጠገንና ጥራትን ለማረጋገጥ በለውጡ ዓመታት መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን አከናውኗል።

በዚህም የትምህርት ተደራሽነትንና ጥራትን በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ተግባራዊ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

ተማሪዎችን በቴክኖሎጂ፣ በእውቀትና በክህሎት ለማብቃት ከዋና ዋና ከተሞች እስከ ገጠር ትምህርት ቤቶች የኮምፒውተር ላብራቶሪዎችን የማደራጀትና የማስፋፋት ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል።

አጠቃላይ የትምህርት ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት።

ዘመኑ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እንደመሆኑ መጠን ይህንን ቴክኖሎጂ ከመማር ማስተማር ሂደቱ ጋር ማጣመር የትምህርት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ሥርዓቱን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ለመደገፍ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።

ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር የመምህራንን የሥራ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ፣ የተማሪዎችንና የመምህራንን ጊዜ በመቆጠብ የትምህርት ጥራትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል።

በተጨማሪም፣ ይህ የፈጠራ ሽግግር የክፍል ውስጥ ትምህርትን ይበልጥ ሳቢና ቀልጣፋ ከማድረጉ በላይ፣ መምህራን በክህሎት የበለጸገ እና ለቴክኖሎጂው ዓለም ዝግጁ የሆነ ትውልድ እንዲያፈሩ ያስችላቸዋል ነው ያሉት።

ቴክኖሎጂ በትምህርት ዘርፍ ላቅ ያለ ሚና ያለው በመሆኑ፣ ሀገራዊ ተደራሽነቱን ለማስፋት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታዋ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026