🔇Unmute
አሶሳ ፤ሀምሌ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የክልሉን እምቅ ሃብቶች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ ክልሉ በብዙ መልኩ መልማት የሚችል እምቅ አቅም ያለው በመሆኑ በዚሁ መሰረት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለይም በማዕድን፣ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጅታላይዜሽን እና ሌሎችም ሴክተሮች እመርታዊ እድገትና ማንሰራራት የታየባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በማዕድን ሃብት ልማትና ተጠቃሚነት ረገድ መሰረታዊ የሚባል ለውጥና ስኬት የተመዘገበበት ነበር ብለዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደመረ አቅም የክልሉን እምቅ አቅሞች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች በክልሉ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026