🔇Unmute
አሶሳ ፤ሀምሌ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የክልሉን እምቅ ሃብቶች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ ክልሉ በብዙ መልኩ መልማት የሚችል እምቅ አቅም ያለው በመሆኑ በዚሁ መሰረት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለይም በማዕድን፣ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጅታላይዜሽን እና ሌሎችም ሴክተሮች እመርታዊ እድገትና ማንሰራራት የታየባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተለይም በማዕድን ሃብት ልማትና ተጠቃሚነት ረገድ መሰረታዊ የሚባል ለውጥና ስኬት የተመዘገበበት ነበር ብለዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደመረ አቅም የክልሉን እምቅ አቅሞች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች በክልሉ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026