የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

‎የክልሉን እምቅ አቅሞች በማልማት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል- ርእሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ ፤ሀምሌ 11/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የክልሉን እምቅ ሃብቶች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፤ ክልሉ በብዙ መልኩ መልማት የሚችል እምቅ አቅም ያለው በመሆኑ በዚሁ መሰረት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለይም በማዕድን፣ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪ፣ በዲጅታላይዜሽን እና ሌሎችም ሴክተሮች እመርታዊ እድገትና ማንሰራራት የታየባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተለይም ‎በማዕድን ሃብት ልማትና ተጠቃሚነት ረገድ መሰረታዊ የሚባል ለውጥና ስኬት የተመዘገበበት ነበር ብለዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተደመረ አቅም የክልሉን እምቅ አቅሞች በማልማት በሁሉም ዘርፎች የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይም የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች በክልሉ ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026