🔇Unmute
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ።
በመኸር አዝመራው ከሚለማው መሬት ከ7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመልክቷል።

በዞኑ የመኸር አዝመራ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በመኸር እርሻ ወቅት ሊለማ የሚችልን መሬት ወደ ልማት በማስገባት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ይሠራል ብለዋል።
በተለይም መሬትን ደጋግሞ በማረስና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት ተሠርቷል ነው ያሉት።
ዞኑ ከቡናና ከሌሎች ቋሚ ሰብሎች ጎን ለጎን በተያዘው መኸር ፈጥነው የሚደርሱና የምግብ ዋስትና ክፍተትን የሚሸፍኑ ሰብሎችም እንደሚለሙ ገልጸዋል።
ለዚህም ምርጥ ዘርና ማዳበሪያን ጨምሮ የግብዓት ስርጭት በወቅቱ እንዲከናወን ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም እንዲያለማም የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደሰ በበኩላቸው፣ በመኸር አዝመራው 44 ሺህ 715 ሄክታር መሬት በሰብል ለማልማት ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።

ከዚህ ውስጥም 26 ሺህ 158 ሄክታር መሬት በአዝዕርት፣ አትክልትና ስራስር ሰብሎች የሚለማ ሲሆን በተለይ ገብስ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ አተር፣ ባቄላና ድንች ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል።
የተቀረው በእንሰትና ፍራፍሬ የሚሸፈን መሆኑን አንስተው በአጠቃላይ ከተያዘው የመኸር አዝመራ ከ7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።
እቅዱን ለማሳካት የማሳ ዝግጅትና የግብዓት ስርጭት መከናወኑን አንስተው በየደረጃው የሚገኝ የግብርና አመራርና ባለሙያ በቅንጅት እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በንቅናቄ መድረኩ የዞንና የሁሉም ወረዳዎች አስተዳዳሪዎች፣ የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026
ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በመንግስት በተከናወኑ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ። ...
Jun 25, 2026