የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ።

በመኸር አዝመራው ከሚለማው መሬት ከ7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተመልክቷል።


በዞኑ የመኸር አዝመራ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ በመኸር እርሻ ወቅት ሊለማ የሚችልን መሬት ወደ ልማት በማስገባት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ይሠራል ብለዋል።

በተለይም መሬትን ደጋግሞ በማረስና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት ተሠርቷል ነው ያሉት።

ዞኑ ከቡናና ከሌሎች ቋሚ ሰብሎች ጎን ለጎን በተያዘው መኸር ፈጥነው የሚደርሱና የምግብ ዋስትና ክፍተትን የሚሸፍኑ ሰብሎችም እንደሚለሙ ገልጸዋል።

ለዚህም ምርጥ ዘርና ማዳበሪያን ጨምሮ የግብዓት ስርጭት በወቅቱ እንዲከናወን ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም እንዲያለማም የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደሰ በበኩላቸው፣ በመኸር አዝመራው 44 ሺህ 715 ሄክታር መሬት በሰብል ለማልማት ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።


ከዚህ ውስጥም 26 ሺህ 158 ሄክታር መሬት በአዝዕርት፣ አትክልትና ስራስር ሰብሎች የሚለማ ሲሆን በተለይ ገብስ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ አተር፣ ባቄላና ድንች ዋና ዋናዎቹ ናቸው ብለዋል።

የተቀረው በእንሰትና ፍራፍሬ የሚሸፈን መሆኑን አንስተው በአጠቃላይ ከተያዘው የመኸር አዝመራ ከ7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ተናግረዋል።

እቅዱን ለማሳካት የማሳ ዝግጅትና የግብዓት ስርጭት መከናወኑን አንስተው በየደረጃው የሚገኝ የግብርና አመራርና ባለሙያ በቅንጅት እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የዞንና የሁሉም ወረዳዎች አስተዳዳሪዎች፣ የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026

በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በአማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ):-በሲዳማ ክልል የሆኮ ወረዳ ነዋሪዎች በመንግስት በተከናወኑ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናገሩ። ...

Jun 25, 2026