የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች ትክክለኛ የልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች - አምባሳደሮች

Jul 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች ትክክለኛ የልማት ጎዳና ላይ እንደምትገኝ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር እና የሥራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁት የኦስትሪያ አምባሳደር ገለጹ።

ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር መቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የምትከተላቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ዓለም አቀፍ ትኩረት እየሳቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያን እየተገበረች እና ዲጂታል ሥርዓትን እያስፋፋች መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለኢኮኖሚያዊ ሽግግር እና ከዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሥርዓት ጋር ለመቀናጀት እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል።

በርካታ የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲና በዲጂታል ሥርዓት እየተሳቡ እንደሚገኙ የገለጹት አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ በኃይል፣ በውሃ እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች ባላት ፖሊሲ ትክክለኛ የልማት አቅጣጫዎች ላይ እየተጓዘች መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ተደራሽነት ማስፋፋትን ጨምሮ ኢትዮጵያ በኃይል አቅርቦት እያሳየች ያለው እመርታዊ ለውጥ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸውን እምነት የሚያጠናክር መሆኑንም ተናግረዋል።

ሀገራቱ በግብርና፣ በጤና፣ በፈጠራና ቴክኖሎጂ፣ በትምህርት እና በምርምር ዘርፎች ላይ የጋራ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራዎችን ማከናወናቸውን አብራርተዋል።

በማህበራዊና ሕዝብ ለሕዝብ ዲፕሎማሲ ረገድም ሀገራቱ ጠንካራ ትብብር እንዳላቸው ያነሱት አምባሳደሩ፤ በጤና፣ በባህል ልውውጥ፣ በንግድ ትስስር እና በቱሪዝም ዙሪያ ያላቸውን ግንኙነት በማሳያነት አንስተዋል።

እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትብብር ይበልጥ ለማስፋት ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል።

የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን እያጠኑ መሆኑን አመልክተው፤ በተለይም በጠብታ መስኖ፣ በሰብል ምርት፣ በአቮካዶ፣ ስንዴ፣ ዓሣ እና የዶሮ እርባታ ባሉ የግብርና ዘርፎች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።

የሥራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁት በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም የኦስትሪያ ባለሀብቶች ወደ ሀገሪቱ እንዲያማትሩ እና አማራጮችን እንዲመለከቱ እያደረገ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማድረግ የጀመረችው ጉዞ በትክክለኛ የዕድገት ጎዳና ላይ እንድትቀመጥ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ በተጨባጭ ኢንቨስት እያደረጉ ያሉ የኦስትሪያ ኩባንያዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የያዘችው ትክክለኛ የልማት ጎዳና ዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን እየሳበ በመሆኑ ማሻሻያው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የኢኮኖሚ ተሳትፎ፣ የትምህርት ትብብር እና የባህል ልውውጥን ጨምሮ የሁለቱ ሀገራት ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ እንደሚጠናከርም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026