የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የጅማ ዩኒቨርሲቲ የባዮጋዝ የምርምር ማዕከል ለአፈር ለምነት እና ለግብርና ምርታማነት እገዛ እያደረገ ነው

Jul 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፡- ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው የባዮጋዝ የምርምር ማዕከል ለአፈር ለምነት እና ለግብርና ምርታማነት እድገት እገዛ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የምርምር ስራዎችን በማከናወን የግብርና ስራን በማዘመን እና በማስፋፋት ዙሪያ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑ ተመላክቷል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ኢንጂነር ኤፍሬም ዋቅጅራ ለኢዜአ እንደገለጹት በዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የተገነባው የባዩ ጋዝ የምርምር ማዕከል ሀይልን ከማመንጨት በተጨማሪ የስልጠና አገልግሎት እየሰጠ ነው።


በዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ይጣል የነበረውን ተረፈ ምርት በመሰብሰብ ባዮ ጋዝ በማምረት ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ማእከሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት የአፈር ለምነት ለመጠበቅና ለግብርና ምርታማነት እድገት እገዛ እንዲያደርግ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ግብርና እና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ ዲን ሰለሞን ቱሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው የግብርና ስራዎችን ውጤታማ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።


በተለይም የምርምር ማዕከሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ ከማሰራጨት በተጨማሪ፣ ዩኒቨርሲቲው በ150 ሄክታር መሬት ላይ ለሚያከናውነው የግብርና ሥራ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የመካኒካል ትምህርት ክፍል መምህርና የባዩ ጋዝ የምርምር ማዕከል ፕሮጀክት አስተባባሪ ሸዋንግዛው ወርቃገኘሁ የምርምር ማዕከሉ በዘርፉ ብቁ ባለሞያዎችን ለማፍራት የስልጠና ማዕከል ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም በሁለተኛ ዲግሪ 18 ተማሪዎች በዘርፉ እየሰለጠኑ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

የባዩ ጋዝ የምርምር ማዕከሉ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመሆን በትብብር እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት አስተባባሪው እንደ ሀገር ባዩ ጋዝን ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲው ታዳሽ ኃይል ምህንድስና ተማሪ የሆኑት ኢየሩስ አንተነህ እና ቤተልሔም አባዲ፤ ባዮ ጋዝ እንዴት እንደሚመረትና ወደ ጠቃሚ ኃይል እንደሚቀየር በተግባር የተደገፈ በቂ እውቀት እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ህብረተሰቡን በተጨባጭ ሥራዎች ለማገልገል የሚያስችላቸውን የማጠናቀቂያ የጥናት ጽሑፍ እያዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌላኛዉ ተማሪ ፊሊጶስ ከፈለኝ በዩኒቨርሲቲው በዘርፉ እያገኘ ያለው እውቀት በምርምር ማዕከሉ ውስጥ በሚሰሩ ተጨባጭ ስራዎች የተደገፈ መሆኑን ተናግሯል።

ተማሪው አክሎም በቀጣይ የኢትዮጵያን የባዩጋዝ ምርት አቅም ለማሳደግ እንደሚሰራ አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026