የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሁሉም ዘርፎች የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ 

Jul 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦በሁሉም ዘርፎች የሕዝቡን ባለቤትነት እና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ በማረጋገጥ የተጀመሩ ውጤታማ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ፡፡

የብልፅግና ፓርት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል።


የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት፤ በሁሉም ክልሎች በሁሉም ዘርፎች የተሻሉ አፈፃፀሞችና ዕድገቶች ተመዝግበዋል፡፡

ከሀገሪቷ ከፍተኛ አቅም እና ከህዝቡ ፍላጎት አኳያ አሁንም ብዙ መሰራት እንደሚጠበቅ በአጽንኦት ገልጸዋል።

ህዝቡ በምርጫ ወቅት የሰጠውን ትልቅ እውቅና ያነሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ አቶ አደም፤ አሁን ላይ እንደ አገልግሎት አሰጣጥ፣ የስራ እድል ፈጠራ እና የኑሮ ውድነት ያሉትን አንገብጋቢ ጉዳዮች በቁርጠኝነት መመለስ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡

የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የገበያ መረጋጋትና የኑሮ ውድነት ቅነሳ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች በመሆኑ በሁሉም የአመራር በንቅናቄ መመራታቸውን ተናግረዋል፡፡

ይህም ከዕቅድ አፈጻጸም በሕዝቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማስቻሉን አመልክተዋል።

ፓርቲው ስራዎችን በህዝብ ንቅናቄ በመምራት ሰባት ዋና ዋና ፋይዳዎች ለማግኘት አስቦ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


በዚህም ችግሮችን በየደረጃው ግብረ-ኃይል በማቋቋም እና መሪዎችን ግንባር ቀደም በማድረግ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በባለቤትነት መምራት ይገባል ብለዋል።

በሁሉም ዘርፍ የህዝቡን ባለቤትነት እና የተደራጀ ተሳትፎ ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመው፤ በተጨማሪም የአስተሳሰብ ፣ የአደረጃጀት፣ የፋይናንስ፣ የግብዓት ማነቆዎችን እና ህገ ወጥ ደላሎችን በመለየት ተጠያቂነትን ማረጋገጥም ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም የንቅናቄ ስራዎችን በሂደት ቋሚና ተቋማዊ በሆነ አሰራር መተካት እንደሚገባም ነው የገለጹት።

የኑሮ ውድነትን ለማቃለል እና ገበያን ለማረጋጋት በማክሮ ኢኮኖሚ ከሚከናወኑ ስራዎች ጎን ለጎን እያንዳንዱ ቀበሌና ወረዳ የራሱን ተጨባጭ ሁኔታ በመጠቀም የምርት አቅርቦትን ማሳደግ፣ የህገወጥ ደላሎችን መረብ መበጣጠስ እና ንግድን በስርዓት መምራት ይኖርበታል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ከውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ጋር ተያይዞ የሚሰጡ ስልጠናዎች እና የምዘና ሂደቶች (COC) ከዓለም አቀፍ ገበያ ፍላጎት ጋር እንዲጣጣሙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026