የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ትኩረት መስጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በጉባኤው የክልሉን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳስታወቁት የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊነትን የተላበሰ እና ከህዝብ ቅሬታ የፀዳ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።


በክልሉ የቤጉ መሶብ እና የአሶሳ መሶብ አንድ ማዕከላት አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልፀው፤ ማዕከላቱ ከ16 ተቋማት የተለዩ 83 አገልግሎቶችን ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በማዕከላቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ39ሺህ በላይ ዜጎች የአገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው በዚህም የላቀ የተገልጋዮች እርካታ ደረጃ ተመዝግቧል ብልዋል።


በክልሉ የመሶብ አገልግሎትን ለማስፋፋት በተያዘው ዕቅድ መሠረት በባምባሲ፣ ከማሺ እና ግልገል በለስ ከተሞች የተገነቡ ማዕከላት በዚህ ወር መጨረሻ ወደ ስራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል።


የክልሉ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥና በመልካም አስተዳደር ላይ የሚነሱ የህዝብ ቅሬታዎችን ለመፍታት በተቋማት ደረጃ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026