🔇Unmute
አሶሳ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ትኩረት መስጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በጉባኤው የክልሉን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳስታወቁት የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊነትን የተላበሰ እና ከህዝብ ቅሬታ የፀዳ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

በክልሉ የቤጉ መሶብ እና የአሶሳ መሶብ አንድ ማዕከላት አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልፀው፤ ማዕከላቱ ከ16 ተቋማት የተለዩ 83 አገልግሎቶችን ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በማዕከላቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ39ሺህ በላይ ዜጎች የአገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው በዚህም የላቀ የተገልጋዮች እርካታ ደረጃ ተመዝግቧል ብልዋል።
በክልሉ የመሶብ አገልግሎትን ለማስፋፋት በተያዘው ዕቅድ መሠረት በባምባሲ፣ ከማሺ እና ግልገል በለስ ከተሞች የተገነቡ ማዕከላት በዚህ ወር መጨረሻ ወደ ስራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል።
የክልሉ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥና በመልካም አስተዳደር ላይ የሚነሱ የህዝብ ቅሬታዎችን ለመፍታት በተቋማት ደረጃ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026