🔇Unmute
አሶሳ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ትኩረት መስጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በጉባኤው የክልሉን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳስታወቁት የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊነትን የተላበሰ እና ከህዝብ ቅሬታ የፀዳ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

በክልሉ የቤጉ መሶብ እና የአሶሳ መሶብ አንድ ማዕከላት አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ገልፀው፤ ማዕከላቱ ከ16 ተቋማት የተለዩ 83 አገልግሎቶችን ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በማዕከላቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ39ሺህ በላይ ዜጎች የአገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመው በዚህም የላቀ የተገልጋዮች እርካታ ደረጃ ተመዝግቧል ብልዋል።
በክልሉ የመሶብ አገልግሎትን ለማስፋፋት በተያዘው ዕቅድ መሠረት በባምባሲ፣ ከማሺ እና ግልገል በለስ ከተሞች የተገነቡ ማዕከላት በዚህ ወር መጨረሻ ወደ ስራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል።
የክልሉ መንግስት በአገልግሎት አሰጣጥና በመልካም አስተዳደር ላይ የሚነሱ የህዝብ ቅሬታዎችን ለመፍታት በተቋማት ደረጃ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እያከናወነ መሆኑንም አንስተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026