🔇Unmute
ጅማ፤ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ) ፡-በጅማ ዞን የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
ከዞኑ ለውጭ ገበያ የሚላክ ተጨማሪ የአቦካዶና ሙዝ ምርት የማጓጓዝ ስራ ዛሬ ተካሂዷል።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት በዞኑ ያለውን መሬትና የውሀ ሀብት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።
አርሶ አደሩን በመደገፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ቡና ሁሉ የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወነ ስራ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል ።
በተለይም ባለፉት ስድስት አመታት የተሻሻሉ የሙዝና የአቦካዶ ዝርያዎችን በማስፋፋት ምርቱን በስፋት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከዞኑ በተጠናቀቀው በጀት አመት 6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኪሎግራም የአቦካዶ እና ሙዝ ምርት ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ 220 ሺህ ኪሎግራሙ ለውጭ ገበያ የቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል ።
በፍራፍሬ ልማቱ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ሆኗል ያሉት አቶ ቲጃኒ በተለይም ወጣቶች በዘርፉ ተደራጅተው ትርፋማ እየሆኑ መምጣታቸውን አመልክተዋል።

የጅማ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም በበኩላቸው አርሶ አደሩ እየቀረበ ባለው የተሻሻለ የፍራፍሬ ዝርያ እና ሞያዊ ድጋፍ ምርቱ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል ።
የጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሀሰን መሀመድ በሚደረግልን ሞያዊ ድጋፍ አቦካዶን በማምረት ከ2014 ዓ. ም ጀምሮ ለዉጪ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆኛለሁ ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026