🔇Unmute
ጅማ፤ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ) ፡-በጅማ ዞን የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
ከዞኑ ለውጭ ገበያ የሚላክ ተጨማሪ የአቦካዶና ሙዝ ምርት የማጓጓዝ ስራ ዛሬ ተካሂዷል።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት በዞኑ ያለውን መሬትና የውሀ ሀብት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።
አርሶ አደሩን በመደገፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ቡና ሁሉ የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወነ ስራ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል ።
በተለይም ባለፉት ስድስት አመታት የተሻሻሉ የሙዝና የአቦካዶ ዝርያዎችን በማስፋፋት ምርቱን በስፋት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
ከዞኑ በተጠናቀቀው በጀት አመት 6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኪሎግራም የአቦካዶ እና ሙዝ ምርት ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ 220 ሺህ ኪሎግራሙ ለውጭ ገበያ የቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል ።
በፍራፍሬ ልማቱ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ሆኗል ያሉት አቶ ቲጃኒ በተለይም ወጣቶች በዘርፉ ተደራጅተው ትርፋማ እየሆኑ መምጣታቸውን አመልክተዋል።

የጅማ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም በበኩላቸው አርሶ አደሩ እየቀረበ ባለው የተሻሻለ የፍራፍሬ ዝርያ እና ሞያዊ ድጋፍ ምርቱ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል ።
የጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሀሰን መሀመድ በሚደረግልን ሞያዊ ድጋፍ አቦካዶን በማምረት ከ2014 ዓ. ም ጀምሮ ለዉጪ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆኛለሁ ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026