የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በጅማ ዞን የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት ተገኝቷል

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ) ፡-በጅማ ዞን የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ውጤት መገኘቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

ከዞኑ ለውጭ ገበያ የሚላክ ተጨማሪ የአቦካዶና ሙዝ ምርት የማጓጓዝ ስራ ዛሬ ተካሂዷል።


የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት በዞኑ ያለውን መሬትና የውሀ ሀብት በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

አርሶ አደሩን በመደገፍና ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ቡና ሁሉ የፍራፍሬ ምርትን ለማሳደግ በተከናወነ ስራ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል ።

በተለይም ባለፉት ስድስት አመታት የተሻሻሉ የሙዝና የአቦካዶ ዝርያዎችን በማስፋፋት ምርቱን በስፋት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።

ከዞኑ በተጠናቀቀው በጀት አመት 6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኪሎግራም የአቦካዶ እና ሙዝ ምርት ለገበያ መቅረቡን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ 220 ሺህ ኪሎግራሙ ለውጭ ገበያ የቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል ።

በፍራፍሬ ልማቱ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ ሆኗል ያሉት አቶ ቲጃኒ በተለይም ወጣቶች በዘርፉ ተደራጅተው ትርፋማ እየሆኑ መምጣታቸውን አመልክተዋል።


የጅማ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ቲጃኒ ተማም በበኩላቸው አርሶ አደሩ እየቀረበ ባለው የተሻሻለ የፍራፍሬ ዝርያ እና ሞያዊ ድጋፍ ምርቱ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል ።

የጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ሀሰን መሀመድ በሚደረግልን ሞያዊ ድጋፍ አቦካዶን በማምረት ከ2014 ዓ. ም ጀምሮ ለዉጪ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆኛለሁ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026