የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለስልጣኑ ሰራተኞች የቡና ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በጉራጌ ዞን በእምድብር ከተማ በሰሜ ቀበሌ አካሄደዋል ።


የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የዋና ዳይሬክተር ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ በወቅቱ እንደገለፁት የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡

ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነት ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።


በዘርፉ በቅንጅት በተሰራው ስራ በቡና ምርታማነት ላይ የተገኘው ውጤት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ይሰራል ብለዋል፡፡

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ቶፊቅ ጁሃር የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረት ስኬት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

በዘንድሮ አመት በክልሉ 48 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


በሽታ የሚቋቋሙ፣ በአጭር ጊዜ የሚደርሱና ምርታማ የሆኑ ዝርያቸው የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ለአርሶ አደሩ እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በብልፅግና ፓርቲ የጉራጌ ዞን ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።


ወጣቶች ቡና በስፋት እና በጥራት በማምረት እንዲሁም በፍራፍሬ ልማት ላይ እንዲሳተፉ መደረጉን ያነሱት ደግሞ የእምድብር ከተማ ከንቲባ አቶ ግንባሩ በርጋ ናቸው ።

የከተማው ወጣት ዳዊት ትእዛዙ በ4 ሄክታር መሬት ላይ ዝርያቸው የተሻሻሉ የቡና ችግኞች እያለማ መሆኑን ተናግሮ ዘንድሮም ይህን በማስፋት ከ2 ሺህ በላይ ችግኝ መትከሉን ተናግሯል፡፡

ሌላው በእምድብር ከተማ በቡና ልማት የተሰማሩት አቶ ሳሙኤል ፍራንሷ በበኩላቸው ባላቸው 3 ሄክታር ማሳ ላይ ቡና እያለሙ መሆኑን ጠቁመው ዘንድሮ ከ1 ሺህ በላይ የተሻሻለ የቡና ችግኝ መትከላቸውን ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026