🔇Unmute
አሶሳ፤ ሐምሌ 19/2018 (ኢዜአ)፡- የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት በመጨረሻ ቀን የጉባዔ ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
ለሁለት ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲመክር የቆየው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት በዛሬው የመጨረሻ ቀን ውሎው ለ2019 በጀት ዓመት 25 ቢሊዮን 424 ሚሊዮን 655 ሺህ 336 ብር በጀት ነው ያጸደቀው።
የረቂቅ በጀቱን ዝርዝር ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዚያድ አብዱላሂ እንደገለፁት በጀቱ የክልሉን ገቢ የመሰብሰብ አቅም ያገናዘበ እና ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚውል ነው ብለዋል።

በጀቱ ለመሠረተ ልማት እና ለትልልቅ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ትኩረት የሰጠ መሆኑን ገልፀው፥ በየደረጃው የሚገኙ አስፈጻሚ አካላትም በጀቱን ለታለመለት ዓላማ ማዋል እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል።
በክልሉ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ እየተሻሻለ በመምጣቱ ከዘንድሮ በጀት 61 ነጥብ 5 በመቶ የሚሆነው በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።
በረቂቅ በጀቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የምክርቤት አባላትም በጀቱን በቁጠባ እና በአግባቡ ተግባር ላይ በማዋል የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን በፍትሃዊነት መፈጸም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ምክርቤቱ በተጨማሪም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለ የገቢ ግብር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅን እና የክልሉን የፋይናንስ አስተዳደርን ለማሻሻል የወጣ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026