🔇Unmute
ሀረር ፤ሐምሌ 21/2018(ኢዜአ)፦ ግብርን በአግባቡና በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን እየተወጡ መሆኑን የሐረሪ ክልል ግብር ከፋዮች ተናገሩ።
የሐረሪ ክልል ታማኝ ለሆኑና ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ላይ ላሉ ነጋዴዎች እውቅና ሰጥቷል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው ግብር ከፋዮች እንዳሉት ግብርን በአግባቡና በወቅቱ በመክፈል የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ ግዴታ እየተወጡ ነው።
ከክልሉ ታማኝ ግብር ከፋዮች መካከል በአይን ህክምና ስራ ላይ የተሰማሩት ዶክተር ኑረዲን አብዲ እንዳሉት፤ የሚጠበቅብኝን ግብር በወቅቱ በመክፈሌ የተሰጠኝ እውቅና ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ ነው።
ከነጋዴው የሚሰበሰበው ግብር ለአካባቢው ልማት መፋጠን የሚውል በመሆኑም ስራዎችን በማሳደግ ለሀገር እድገትይበልጥ አስተዋጽኦ ለማድረግ እንደሚሰሩ ነው የገለጹት።
ግብርን በአግባቡ መክፈል ለመጪው ትውልድ ምቹ የሆነች ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥም የራስን አሻራ ለማኖር የማያስችል ነው ብለዋል።
በከተማው በሆቴል ስራ የተሰማሩት አቶ ሃይሉ ካሳ እና ወይዘሮ ዩስራ መሀመድ በበኩላቸው፤ ግብር መክፈል ለሀገር ልማትና እድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በመገንዘብ የዜግነት ግዴታችን በመወጣት ላይ ነን ብለዋል።
በተለይም'' በአሁኑ ወቅት በሚካሔዱ የልማት ስራዎች ተጠቃሚ በመሆናችን በወቅቱ በተገቢው መንገድ ወደንና ፈቅደን በሚፈለገው መንገድ ግብራችንን መክፈልን እንቀጥላለን'' ነው ያሉት።
በክልሉ መንግስት የተሰጣቸው እውቅናም ይበልጥ ለመስራትና ለሌሎች አርአያ ለመሆን እንዳነሳሳቸው አመልክተዋል፡፡

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን አብዱላሂ እንደገለጹት፤ በክልሉ በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የታክስ ተገዢነትን በማሳደግ የክልሉን የልማት ወጪ በራስ ገቢ ለመሸፈን በማቀድ ወደ ስራ ተገብቷል።
በተለይ የታክስ ህጎችን ወደ ስራ በማስገባት ፍትሃዊ የግብር ክፍያዎች እየተፈጸሙ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና ለውጥ እየተመዘገበበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በዘንድሮ በጀት ዓመት በክልሉ ከተለያዩ የገቢ ርዕሶች ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አመልክተዋል።
በቀጣይም የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን የማዘመን እና የንግዱ ማሕበረሰብ በታክስ አሰባሰቡ ሒደት ላይ ግንዛቤውን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026