የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የአማራ ክልል ምክር ቤት ለአዲሱ በጀት ዓመት ከ402 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ በጀት መርምሮ አጸደቀ

Aug 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሐምሌ 25/2018(ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል ምክር ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለሚካሔዱ የልማት ዕቅዶች ማስፈጸሚያ የሚውል ከ402 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ በጀት መርምሮ አጽድቋል።

የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በሦስተኛ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በመምከር እና የአዲሱነ በጀት ዓመት የዕቅድ ማስፈጸሚያ በጀት በማጽደቅ ተጠናቋል።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ አታላይ ጥላሁን የበጀት ረቂቁን ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ በጀቱ የክልሉን ህዝብ የመልማት ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው።

ከበጀቱ ውስጥ ከ286 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ የሚሆነው በክልሉ ከሚሰበሰብ ገቢ የሚሸፈን ሲሆን 111 ቢሊየን የሚጠጋው ደግሞ ከፌደራል መንግስት ጥቅል የቀመር መደበኛ ድጋፍ የሚገኝ ነው ብለዋል።

ቀሪው ከዘላቂ ልማት ግቦችና መሰል የፋይናንስ ምንጮች በሚገኝ ሀብት የሚሸፈን እንደሆነም ተናግረዋል።


የበጀት ድልድሉ ሊኖሩ የሚችሉ ለውጦችን፣ የመዋቅር ማሻሻያዎችን፣ ብሎም ወረዳዎችና ከተሞች የድህነት ተኮር ዘርፍ ያለባቸውን የካፒታል በጀት ውስንነት መሰረት የተደረገ ነው ብለዋል።

የተመደበው በጀት ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ176 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ወይም 78 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በጀቱ የክልሉን ህዝብ የላቀ የልማት ጥያቄ ፍላጎት መሰረት በማድረግ የቀረበ እንደሆነም አብራርተዋል።

የቀረበውን በጀት የህዝብን የልማት ጥያቄ በአግባቡ ሊመልስ በሚችል አግባብ ለታለመለት ዓላማ በቁጠባ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ለስኬታማነቱም በየደረጃው ያለው ባለድርሻ አካል የድርሻውን መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026