🔇Unmute
ባምባሲ፤ ሐምሌ 28/2018 (ኢዜአ)፦በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ በክልሉ ሶስተኛውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በባምባሲ ከተማ መርቀው ስራ አስጀምረዋል።

ርዕሰ መስተደድሩ በወቅቱ እንደገለፁት፤ ማዕከሉ የተለያዩ የመንግሥትና የልማት አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ በማቀናጀት የተገልጋዩን እንግልት፣ ጊዜና አላስፈላጊ ወጪ የሚቀንስ ነው።
ማዕከሉ የመንግስትን አሰራር ዘመናዊና ቀልጣፋ በማድረግ ትልቅ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ ይህም ሌብነትና ብልሹ አሠራርን በመከላከል ግልጽ እና ፍትሐዊ አሰራርን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
ማዕከሉ ከከተማዋ ዕድገት ጋር የተመጣጠነ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በዘመናዊ እና በተቀላጠፈ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝም ገልጸዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፥ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የዜጎችን የአገልግሎት እርካታ ያሳደገ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን የመለሰ ኢንሼቲቭ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋት በተቋማት የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፤ በቅርቡ በግልገል በለስ እና ከማሺ ከተሞች ተመሳሳይ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ እንደሚጀምር አስታውቀዋል።
የባምባሲ መሶብ የአንድ ማዕከል አራት የከተማ አስተዳደር ሴክተሮችን እንዲሁም ሶስት የፌደራል ተቋማትን ጨምሮ 36 አገልግሎቶችን በአንድ ላይ መስጠት የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አስካለች አልቦሮ፣ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር እንዲሁም የባምባሲ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026