🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 4 /2018(ኢዜአ)፦ ወጣቶች ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል በመራመድ ራሳቸውን በክህሎት ብቁ እንዲያደርግ የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ ጥሪ አቀረበች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቀረበውን የኢትዮጵያ ወጣቶች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭን እንዲቀላቀሉ እና የክረምቱ ወቅት ከመጠናቀቁ በፊት የተሳታፊዎችን ቁጥር ወደ 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተደረገውን ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት በኢኒሼቲቩ ዙሪያ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በመቀጠል በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ልምዳቸውንና እይታቸውን ያካፈሉ አራት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ላይ ታሪኳን ያካፈለችው የቴክኖሎጂ ሥራ ፈጣሪዋ ቤተልሔም ደሴ፤ የቴክኖሎጂ ሕይወቷ ከአስራ ሰባት ዓመት በፊት ገና የአስር ዓመት ታዳጊ ባለችበት ወቅት እና የዲጂታል አማራጮች ጨርሶ በሌሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደተጀመረ ገልጻለች።
ያለፈውን ጊዜ ከአሁኑ ጋር በማነጻጸርም፣ ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ በስፋት ተደራሽ በመሆኑ የአሁኑ ዘመን ወጣቶች ህልማቸውን ለማሳካት የሚያስችል ምቹ መንገድ እንዳላቸው አመላክታለች።
ይህ ትልቅ ዕድል ቢኖርም ስኬት ግን ፈጣን እርምጃን እንደሚጠይቅ ያስገነዘበችው ቤተልሔም፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከመጠባበቅ ወጥተው አሁኑኑ የለውጥ መሪ እንዲሆኑ፣ እንዲሁም ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር እኩል ለመራመድ ራሳቸውን በክህሎት በንቃት እንዲያበቁ ጥሪዋን አስተላልፋለች።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለመመዝገብ፦ ethiocoders.et
#PMOEthiopia #DigitalEthiopia2030 #5MillionEthiopianCoders
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026