የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በከተሞቹ የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል

Aug 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ) ፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሆሳዕና፣ በቡታጅራና በወልቂጤ ከተሞች የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የተለያዩ የልማት ስራዎች መከናወናቸው ተመላከተ፡፡

የከተሞቹ አስተዳደሮች ከንቲባዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አገልግሎትን ለማዘመን የሚያስችል መሶብ የአንድ ማዕከል፣ የጤና ተቋማት፣ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገድ እና የ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል ብለዋል፡፡

ይህም ከተማዋን ጽዱ፣ ውብና ለነዋሪው ምቹ፣ ለኢንቨስትመንትና ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ተመራጭ እንድትሆን አስችሏል ነው ያሉት።

የከተማው ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ መሰብሰብና የማህበረሰቡን ተሳትፎ ማዕከል ያደረጉ ስራዎችን ተግባራዊ የማድረጉ ሂደት በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ በበኩላቸው፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ የልማት ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ተናግረዋል።

አስተዳደሩ የማህበረሰቡን ተሳትፎና የውስጥ አቅምን በመጠቀም ተግባራዊ በማድረግ ላይ ከሚገኘው የ25 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥ 11 ነጥብ 26 ኪሎ ሜትሩ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ነው ያሉት።

ይህም ከተማዋን ለኑሮ ምቹ፣ ሳቢና ማራኪ ከማድረግ ባለፈ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዋ እንዲነቃቃ ማድረጉን ገልጸዋል።

በከተማው እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ወልቂጤን ለነዋሪዎቿ ምቹና ተመራጭ እንድትሆን አድርጓታል ያሉት ደግሞ የከተማዋ ከንቲባ ሙራድ ከድር ናቸው።


በልማት ስራውም የማህበረሰቡ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን እንዲሁም የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በ2019 ዓ/ም የትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር በቡታጅራ ከተማ የምክክር መድረክ ማካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026