የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የቤቶች ልማት ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ አካታች አካሄድ ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Aug 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 12/2018 (ኢዜአ)፦ የቤት ልማት ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ አካታች አካሄድ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንየከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት አዋጅ ቁጥር 1388/2017 ቀደም ሲል መጽደቁ ይታወሳል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር በአዋጁ መሠረት የተዘጋጀውን መመሪያ የማስተዋወቂያ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር የማስተዋወቅ ውይይት አካሂዷል።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፣ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤቶችን አቅርቦት ለማስፋት ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ የቤት አቅርቦት አማራጮችን ለማስፋት እየተሠራ ነው።

የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችለው መመሪያ የቤት ልማት ኢንቨስትመንትን ለማሳደግና በሁሉም አካባቢዎች ተመጣጣኝ ዕድገትን ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

ሀገራት ተጨማሪ የካፒታል ኢንቨስትመንት ለማሳደግ የውጭ ዜጎችን የቤት ባለቤት ማድረግን እንደ አንድ መንገድ እንደሚጠቀሙ ጠቁመው፣ በኢትዮጵያም ኢኮኖሚውን ክፍት በማድረግ የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አዋጅ መውጣቱን አንስተዋል።

የቤት ልማት አቅርቦትን ማሳደግ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማስፋት፣ የሥራ ዕድልን ማስፋትና የክልል ከተሞች ተመጣጣኝ ዕድገት እንዲያስመዘግቡ ማድረግ ከአዋጁ ጠቀሜታዎች መካከል እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

አዋጁን ለመተግበር የተዘጋጀውን መመሪያ መሠረት በማድረግ ሁሉም ተቋማት ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ማድረግና ወደ ተቀናጀ እንቅስቃሴ መግባት ያስፈልጋል ብለዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ጸጋዬ ሞሼ ባቀረቡት ማብራሪያመመሪያው ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመውሰድ የውጭ ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ሥርዓት ለመዘርጋትና ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ያለመ ነው ብለዋል።

በአዲስ አበባና ሸገር ከተሞች የውጭ ዜጎች የቤት ባለቤት ለመሆን ከሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች አንዱ ዝቅተኛው የግዥ ዋጋ 150 ሺህ ዶላር ሲሆን፣ በሌሎች ክልሎች ከተሞች ደግሞ ከ100 ሺህ እስከ 120 ሺህ ዶላር መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም ከወንጀል ነፃ ማረጋገጫ፤ የሰላምና ደኅንነት ማረጋገጫ ሰነዶች፣ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን የተሰጠ ሕጋዊ የኢንቨስትመንት ፈቃድና የጽሑፍ ማረጋገጫ፣ ፓስፖርትና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።

በመመሪያው አተገባበር ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ውይይት፣ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትንና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተጠቅሷል።

ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመግታትና ሕገ-ወጥ አሠራርን ለመከላከል የፋይናንስ ደኅንነትና ቁጥጥርን ለማጠናከር እንደሚሠራና የመመሪያ ጥሰት በሚፈጽሙ አካላት ላይ ጠንካራ ተጠያቂነት እንደሚኖር ተነስቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026