የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ለገበያው መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ የሚገኙት የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች

Aug 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብና ገበያን በማረጋጋት ጉልህ ጠቀሜታ እያስገኙ መሆኑን ሸማቾችና ምርት አቅራቢዎች ገለጹ።

መንግሥት ገበያውን ለማረጋጋት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ማደራጀት አንዱ ሲሆን፣ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ማኅበረሰብ እንዲደርሱ እያስቻለ ነው።

ገበያዎቹ አርሶ አደሮችና አነስተኛ አምራቾች ከደላላ ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለተጠቃሚው እንዲያቀርቡ በማስቻል የገበያ ትስስርን አጠናክረዋል።

ይህም ለአምራቾች የተሻለ ገቢ እንዲፈጠር፣ ለተጠቃሚዎች ደግሞ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ በማድረግ የገበያ መረጋጋትን እያጎለበተ ይገኛል።

ኢዜአ በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ሲሸምቱ ያነጋገራቸው ሸማቾች እንደገለጹት፣ ገበያዎቹ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በዓይነት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በአቅራቢያቸው ማግኘት አስችለዋቸዋል።

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል ወይዘሮ ሶስና ገብረሚካኤል እንዳሉት፤ ገበያው በአቅራቢያቸው መከፈቱ ቀደም ሲል መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን ለመሸመት ይባክን የነበረውን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ ቀንሷል።

"አሁን የቅዳሜና እሁድ ገበያው በአቅራቢያችን በመኖሩ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት ችያለሁ" ብለዋል።

መንግሥት በየአካባቢው ያስጀመራቸው የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እንግልትንና ወጪን በመቀነስ፣ የኑሮ ውድነትን ለማስታገስና ገበያን ለማረጋጋት የወሰደው ወሳኝ እርምጃ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በቀጣይም መንግሥት የሰብልና መሰል ምርቶችን በብዛትና በጥራት በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እንዲቀርቡ በማድረግ፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ተጠቃሚ የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ዝናሽ ወጋየው፤ በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የሚቀርቡ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች ጥራት ያላቸውና ከመደበኛው ገበያ ከ20 በመቶ በላይ ቅናሽ ያላቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።

መሰል ገበያዎች ለሸማቾች በቅርብ ከመገኘታቸው ባለፈ፣ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት የሚያስችሉ በመሆናቸው መጠናከር እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

የቅዳሜና እሁድ ገበያዎቹ የሸማቾችን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ በመቆጠብ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከማበርከታቸው ባለፈ ለዋጋ ንረት መረጋጋት ዓይነተኛ መፍትሔ መሆናቸውን አክለዋል።

በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የፍጆታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸው ለማኅበረሰቡ እፎይታ እየሰጠና የኑሮ ውድነትን እያረጋጋ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ ወይዘሮ ቃልኪዳን ሰለሞን ናቸው።

ገበያዎቹ በየዕለቱ የምንጠቀምባቸውን መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች በአቅራቢያችን እንድናገኝ አስችለውናል ሲሉም ገልጸዋል።

በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ምርቶችን ለሽያጭ ይዘው ከቀረቡት መካከል ወጣት ሄኖክ ተሰማ፤ ምርቶችን በቀጥታ ከማሳ በማምጣት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች እያቀረቡ እንደሚገኝ ገልጿል።

አንዋር ሰዒድ በበኩላቸው፤ በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የሚገበዩ ሸማቾች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ ምርቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026