የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ለአዲስ ዓመት በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይኖርና ሕገ ወጥ ግብይትን ለመቆጣጠር ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል

Sep 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 26/2018 (ኢዜአ)፦ በመጪው የአዲስ ዓመት በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰትና ሕገ ወጥ ግብይትን ለመቆጣጠር አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ አስታወቁ።

የቢሮ ኃላፊዋ ሀቢባ ሲራጅ የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፣ ለአዲስ ዓመት በዓል ግብይት መሳለጥ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል።

የበዓሉ ወቅት ከፍተኛ የገበያ ፍላጎትን መነሻ በማድረግ ሊከሰቱ የሚችሉ የዋጋ ጭማሪ፣ የምርት እጥረትና ሕገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም የበዓል ገበያን ለማረጋጋት 7 የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የፋብሪካ ምርቶች መሸጫ፣ 5 የእንስሳት ቄራ ማዕከላትና 264 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ሳምንቱን ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።

በአዲስ አበባ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽንና በኅብረት ሥራ ማኅበራት ትብብር ጤፍ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የእርድ እንስሳት፣ ዶሮዎችና እንቁላል፣ የምግብ ዘይትና ሌሎች አስፈላጊ ምርቶች በስፋት ለገበያ እንደሚቀርቡ አስረድተዋል።

በበዓሉ ወቅት ሰው ሠራሽ የምርት እጥረት በሚፈጥሩና ዋጋ በሚጨምሩ ሕገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ ቁጥጥር በማድረግ አስፈላጊውን አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስበዋል።

የመጋዘን ፍተሻ፣ የመለኪያ መሣሪያዎች ትክክለኛነት፣ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸው ምርቶችን የማረጋገጥና የመቆጣጠር ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።

ኅብረተሰቡም በዓሉን ምክንያት በማድረግ በግብይት ሥርዓቱ ላይ አሻጥር በመሥራት የሕግ ጥሰትና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ሲመለከት በነጻ ስልክ ቁጥር 8588 ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026