የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ 

Sep 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መሶብ የአንድ ማዕከል፤ የመደመር መንግሥት የአገልግሎት ትራንስፎርሜሽን ማስፈንጠሪያ

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የተጀመረው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ የዜጎችን እንግልት በመቀነስና የመንግሥት አሰራርን በማዘመን ረገድ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ይገኛል።

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን፣ የወረቀት ስራንና እንግልትን በማስቀረት ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት የተዘረጋ ስርዓት ነው።

ፕሮጀክቱ አገልግሎት ፈላጊዎች በአንድ ማዕከል በርካታ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፤ ይህም ህብረተሰቡ የመሬት አስተዳደር፣ የኢንቨስትመንት፣ የገቢዎችና ሌሎችንም የመንግሥት አገልግሎቶች በኦንላይንና በአካል ማግኘት የሚያስችል ነው።

አገልግሎቱ በአዲስ አበባ፣ በአዳማ፣ በባህር ዳር እና በሌሎችም የክልሎች ከተሞች ተግባራዊ መሆን የጀመረ ሲሆን፤ ማዕከላቱን በየደረጃው እስከ ወረዳ ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተንቀሳቃሽ መሶብ አገልግሎትን በአዲስ አበባ ባስጀመሩበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የቆዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎችን በመፍታት የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውታል።

ይህንን ለማሳካት በመንግሥት፣ በግል ኩባንያዎችና በእያንዳንዱ ዜጋ ዘንድ የባህልና የአስተሳሰብ ለውጥ መምጣት እንዳለበትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

ሀገሪቷን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መንግሥት በትኩረት እየሰራባቸው ካሉ አምስት የኢኮኖሚ አምዶዎች መካከል ቴክኖሎጂ አንደኛው መሆኑን ነው በወቅቱ ያብራሩት።

ቴክኖሎጂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የቱሪዝም ዘርፍን ለማዘመን እንዲሁም ዲጂታል የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ሁሉንም የልማት ዘርፎች የሚያቀናጅ ዋና መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ሲሆን፤ በተለይም የአገልግሎት አሰጣጥን ወደ ዘመናዊና ዲጂታል ሥርዓት በመቀየር የዜጎችን እንግልት መቀነስ አስችሏል።

የ“ዲጂታል 2030” ስትራቴጂ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተገኙ ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሀገራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግርም አብራርተዋል።

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መሶብ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ ባሉ ከ108 በላይ ማዕከላት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ተችሏል።


የአገልግሎቱ አጠቃላይ ሀገር አቀፍ የተገልጋዮች እርካታ መጠን ከ99 በመቶ በላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።

በዘመናዊ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጫዎች ማዕከላት በአካል መጥተው መገልገል ለማይችሉ ዜጎች አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አጽንኦት መስጠታቸው ይታወሳል።

በመዲናዋ የተዘረጋው የዲጂታል መሶብ አገልግሎት፣ በከተማ ደረጃ እየተካሄደ ላለው የዲጂታል ሽግግር ማሳያ ከመሆኑም በላይ በነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026