የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነትና የጽናት ተሞክሮ ለቀጣይ ትላልቅ ፕሮጀክቶች መሠረት ይሆናል

Sep 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጳጉሜን 3/2018 (ኢዜአ)፡-የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እውን ያደረገው የኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረትና ጽናት ተሞክሮ በቀጣይ ለሚከናወኑ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች መሰረት እንደሚሆን የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አረጋዊ በርሔ(ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት ከአንድ ተቋም ወይም ከአንድ ቡድን ጥረት የመነጨ ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የጋራ ተሳትፎና ትብብር ውጤት ነው።

ኢትዮጵያ በርካታ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ያሏት በመሆኑ የውሃ ሀብቷን በአግባቡ በመጠቀም ተጨማሪ የውሃና የኃይል ልማት ፕሮጀክቶችን ማልማት እንደምትችልም ገልጸዋል።


የውሃ ሀብትን ለኃይል ማመንጫነት በማዋል የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎትን ከማሟላት ባሻገር ለቀጣናው ሀገራት ኤሌክትሪክ ሀይል በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘት የሚያስችል እምቅ አቅም አለ ነው ያሉት።

ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ ልማት ለመቀየር ዋነኛው መሠረት የሕዝብ ትብብርና ተሳትፎ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም ትልቅ ሀገራዊ ዓላማዎችን ማሳካት እንደሚቻል የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተሞክሮ ትልቅ ማሳያ መሆኑን አመልክተዋል።

ዋናው ቁልፉ ነገር መተባበር እንደሆነ አመልክተው፣ በልማት ላይ ትኩረት ከተደረገ ኢትዮጵያን ትልቅ የልማትና የሥልጣኔ ደረጃ ላይ ማድረስ እንደሚቻልም ገልጸዋል።


የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን እውን ለማድረግ የታየው የህዝብ ጽናት ታሪካዊ መሆኑን ጠቁመው፤ የተገኘው ተሞክሮ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት ኢትዮጵያውያን በአንድነት እና በጽናት ሲቆሙ ትልቅ ሀገራዊ ዓላማን ማሳካት እንደሚችሉ ያሳየ እንደሆነ አመልክተው፤ ይህ የትብብር እና የጽናት መንፈስ በቀጣይ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026