የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባለፉት ስምንት ዓመታት በውጭ ዕዳ ጫና ቅነሳ፣ በውጭ ምንዛሬ አስተዳደርና በዋጋ ንረት ቅነሳ ትርጉም ያለው ውጤት ተመዝግቧል

Jun 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በውጭ ዕዳ ጫና ቅነሳ፣ በውጭ ምንዛሬ አስተዳደርና በዋጋ ንረት ቅነሳ ትርጉም ያለው ውጤት ማምጣቱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እየብ ተካልኝ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ሀሳብ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ በሳይንስ ሙዚየም ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እየብ ተካልኝ (ዶ/ር) ባለፉት ስምንት ዓመታት በሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በተወሰዱ እርምጃዎች የተገኙ ውጤቶች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ በግብርና፣ ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝምና ዲጂታል መስኮች ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገብ ማስቻሉን አንስተዋል።

ከለውጡ በፊት የውጭ ዕዳ ጫና ከፍተኛ እንደነበር አስታውሰው፤ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲሁም ከመደበኛው የዶላር ምንዛሬ የጥቁር ገበያው ምንዛሬ በከፍተኛ ደረጃ መብለጡ ትልቅ ችግር እንደነበር አንስተዋል።

ሪፎርሙ የዕዳን ጫናን ለመቀነስ ከማስቻሉም ባሻገር የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግሮች እንዲቀረፉ ማድረጉን አመልክተዋል።

የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ የውጭ ምንዛሬን ገበያ መር በማድረግ፣ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲን በማዘመን ትርጉም ያለው ውጤት ተገኝቷል ብለዋል።

በዚህም የፋይናንስ ዘርፉን የሚያጠናክሩ ተግባራት ተከናውነዋል ያሉት ገዥው ለዘላቂና አካታች ዕድገት ጠንካራ መሠረት ተጥሏል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበቱ እስከ 34 በመቶ የደረሰበት ጊዜ እንደነበር ያስታወሱት እዮብ (ዶ/ር) በተወሰደው የማሻሻያ እርምጃ የዋጋ ግሽበቱን ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ መቻሉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ንግድ ገቢ እያደገ መምጣቱን ገልጸው ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ተወዳዳሪነት እየጨመረ ነው ብለዋል።

ይህም የተወሰደው የማሻሻያ ውጤት መሆኑንም በማብራሪያቸው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026