የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ተሰራጭቷል

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ስርጭት መከናወኑን የክልሉ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ።

በቢሮው የኢነርጂ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሶሬሳ እንደገለጹት፤ በክልሉ በቤተሰብ ደረጃ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ አማራጭ የኃይል አቅርቦት ላይ በትኩረት እየተሠራ ነው።


በዚህም ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የሶላር ፓኔል ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አባወራዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል።

የታዳሽ ኃይል ልማትና ተደራሽነት የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ከዋናው የኃይል ቋት ርቀው የሚገኙ የገጠር የጤናና የትምህርት ተቋማት የኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


በተጨማሪም በናፍጣ የሚሠሩ የውኃ ተቋማትን ወደ ፀሐይ ኃይል በመቀየር ኅብረተሰቡ ዘላቂ የመጠጥ ውኃ አገልግሎት እንዲያገኝ መሠራቱንም ጠቁመዋል።

በተያያዘም ከ700 ሺህ በላይ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችንና ከ1 ሺህ 500 በላይ የባዮ ጋዝ በመሥራት ለመብራት አገልግሎት እንዲሁም ተረፈ ምርቱ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ እንዲውል መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026