የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዶሮ፣ በወተት፣ በእንቁላል፣ በአሳና ሌሎች ምርት ልማት ላይ መሠረታዊ ለውጥ እያመጣ ነው

Jun 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፦ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በዶሮ፣ በወተት፣ በእንቁላል፣ በአሳና በሌሎች ምርት ልማት ላይ መሠረታዊ ለውጥ እያመጣ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ ገለጹ፡፡

ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ በተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሐ-ግብር፣ ቀደም ሲል ትኩረት አጥቶ የነበረውን የእንስሳት ተዋጽኦ ልማት በቅንጅትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ አሁን ላይ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ይገኛል።

በዚህም መርሐ-ግብሩ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት እምርታን በተግባር በማሳየት የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነትና የዜጎችን ክብር ለማረጋገጥ የተጣለውን ግብ እያሳካ ይገኛል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ፤ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት ለማሳካት የእንስሳት ሀብት ልማት ሚና ጉልህ መሆኑን ገልጸዋል።


በ2018 በጀት ዓመት የገበያ ፍላጎትን መነሻ በማድረግ የእንስሳት ምርታማነትንና ጤናን ለማጎልበት የዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻልና ማዳቀል ሥራዎች በስፋት መከናወናቸውን አስታውቀዋል።

በዚህም 4 ነጥብ 9 ሚሊዮን የወተት ላሞችን ለማዳቀል የተያዘው እቅድ እየተሳካ ሲሆን፣ 160 ሚሊዮን ጫጩቶችን ለማሰራጨትና 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን እንቁላል ለማምረት የተያዘው ግብም በውጤታማነት እየሄደ ይገኛል ብለዋል፡፡

ሚኒስቴሩ የዶሮ ምርትን ለማሳደግ 4 ዘመናዊ የጫጩት ማስፈልፈያ ማሽኖችን ለክልሎች ያሰራጨ ሲሆን፣ ተጨማሪ 11 ማሽኖችን ለመግዛት በሂደት ላይ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

በተጨማሪም በኩሬዎችና በሰው ሠራሽ ሐይቆች የአሳ ምርት ልማት በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ የእንስሳት ጤናን ለመጠበቅ አዳዲስ አሠራሮች፣ የተጠናከረ የክትባት ስርጭት እና የኤክስቴንሽን አገልግሎት በመዘርጋቱ ዘርፉን በተገቢው መንገድ ለማልማት የሚያስችል ትልቅ አቅም ተፈጥሯል ብለዋል።

በተለይም ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች በሚገኙባቸው የአርብቶ አደር አካባቢዎች የድንበር ዘለል በሽታዎችን ለመቆጣጠር ክትባት በስፋት መሰጠት የተጀመረ ሲሆን፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የመሥራት ባህልም እያደገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


ባለፉት ዓመታት በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የተከናወኑ ተግባራት የእንስሳትን ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ ማላቃቸውን ገልጸዋል።

ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በሀገሪቱ የነበረው የእንቁላል ማምረት አቅምበዓመት ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ወደ 11 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ የወተት ምርት ደግሞ በዓመት ከ7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ወደ 16 ቢሊዮን ሊትር ማደጉን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማፋጠን ትልቅ አቅም መፍጠራቸውንም አስረድተዋል።

የእንስሳት ምርታማነትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የመኖ አቅርቦትን ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ማሽኖችን ገዝቶ ለክልሎች ማሰራጨቱንና የግሉ ዘርፍ ፋብሪካዎችም እገዛ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026