🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ አዲሱ ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ስትራቴጂ እና ፍኖተ ካርታ የህብረት ሥራ ማህበራትን አሠራር ዘመናዊ በማድረግ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።
የግብርና ሚኒስቴር የአስር ዓመት ሀገር አቀፍ የህብረት ሥራ ስትራቴጂ እና ፍኖተ ካርታ የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ አዲሱ ፍኖተ ካርታ የህብረት ሥራ ማህበራትን አሠራር ዘመናዊ በማድረግ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው።
ማህበራቱን በስፋት በማደራጀትና ተወዳዳሪነታቸውን በማሳደግ የገጠርና የከተማ ትስስርን ማጠናከር እንደሚቻል ገልጸው፣ ይህም ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ስትራቴጂውና ፍኖተ ካርታው በዋናነት በርካታ ጠቀሜታዎችን እንደሚያስገኝ ጠቁመው የግብርና ሽግግርን በማፋጠን፣ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ከፍ ያደርጋል ብለዋል።
በተጨማሪም የህብረት ሥራ ማህበራትን የሚያዘምን መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ የህብረት ሥራን ማዘመን ግብርናን ማዘመን ነው፤ግብርናን ማዘመን ደግሞ የሀገርን ኢኮኖሚ ማረጋገጥ ነው ሲሉ አስገንዝበዋል።

ከዚህ ቀደም በህብረት ሥራ ማህበራት ውስጥ ሲያጋጥሙ የነበሩ መዋቅራዊና አሠራራዊ ተግዳሮቶችን በመቅረፍ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ያስችላልም ብለዋል፡፡
ስትራቴጂው ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ሲገባ ምርትና ምርታማነትን በማረጋገጥ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሪ እንደሚያስገኝም ጠቁመዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍ የሚያድርግ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ይህ አገር አቀፍ የአስር ዓመት ስትራቴጂና ፍኖተ ካርታ የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚን በማፋጠን፣ ማህበራቱ በሀገር ውስጥ ምርት ሥርጭትና በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የጎላ እንደሚያደርገው በንቅናቄ መድረኩ ላይ ተመልክቷል።
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026