የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ሸዋ ዞን በተያዘው የመኸር ወቅት 31 ሺህ ሄክታር መሬት በሩዝ ይለማል

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን በተያዘው የመኸር እርሻ 31 ሺህ ሄክታር መሬት በሩዝ የማልማት ስራ መጀመሩን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።

የክልል፣ የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በዞኑ ኢሉ ገላን ወረዳ የ2018/19 የምርት ዘመን ሩዝን በኩታ ገጠም የማልማት ስራ ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ እንደገለጹት፤ በክልሉ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ ተቀርጾ ወደ ስራ ከገቡት 33 ኢኒሼቲቮች መካከል የሩዝ ምርት አንዱ ነው።


የሩዝ ምርት በዞኑ በስፋት ያልተለመደ ቢሆንም፣ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ህብረተሰቡ በአንድነት በኩታ ገጠም ተደራጅቶ ወደ ስራው መግባቱን ጠቅሰዋል።

ዘርፉ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ማሳደግ የሚችል በመሆኑ፣ በ36 ሄክታር መሬት ላይ የሩዝ ዘር መዘራት መጀመሩን ገልጸዋል።

የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲሳ ሀይሉ በበኩላቸው በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ለመሸፈን ታቅዷል ብለዋል።


ከዚህ ውስጥ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነውን መሬት በሩዝ ምርት ለመሸፈን ታቅዶ ስራው ተጀምሯል ብለዋል።

የኢሉ ገላን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በንቲ በበኩላቸው፣ የወረዳው አርሶ አደሮች የሩዝ ምርት የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴን እየተላመዱ መምጣታቸውን ገልጸዋል።


በወረዳው በ2018/19 የምርት ዘመን 5 ሺህ ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት ለመሸፈን ታቅዶ፣ የግብርና ግብዓቶችን ለአርሶ አደሮቹ በማቅረብ ዘር የመዝራት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

ከወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ዘውዱ ዘነበ፤ የሩዝ ሰብልን በኩታ ገጠም መዝራት ከጀመሩ አራት ዓመታት እንደሆናቸው ገልጸው፣ ቀደም ሲል ከሄክታር አነስተኛ ምርት ያገኙ እንደነበር አስታውሰዋል።


በአሁኑ ወቅት ግን በግብርና ባለሙያዎች በሚደረግላቸው ሙያዊ ድጋፍ ታግዘው ከአንድ ሄክታር ማሳቸው እስከ 80 ኩንታል የሩዝ ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026