🔇Unmute
አምቦ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን በተያዘው የመኸር እርሻ 31 ሺህ ሄክታር መሬት በሩዝ የማልማት ስራ መጀመሩን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።
የክልል፣ የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በዞኑ ኢሉ ገላን ወረዳ የ2018/19 የምርት ዘመን ሩዝን በኩታ ገጠም የማልማት ስራ ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲዳ ጉደታ እንደገለጹት፤ በክልሉ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ ተቀርጾ ወደ ስራ ከገቡት 33 ኢኒሼቲቮች መካከል የሩዝ ምርት አንዱ ነው።

የሩዝ ምርት በዞኑ በስፋት ያልተለመደ ቢሆንም፣ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ህብረተሰቡ በአንድነት በኩታ ገጠም ተደራጅቶ ወደ ስራው መግባቱን ጠቅሰዋል።
ዘርፉ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ማሳደግ የሚችል በመሆኑ፣ በ36 ሄክታር መሬት ላይ የሩዝ ዘር መዘራት መጀመሩን ገልጸዋል።
የምዕራብ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲሳ ሀይሉ በበኩላቸው በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ለመሸፈን ታቅዷል ብለዋል።

ከዚህ ውስጥ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነውን መሬት በሩዝ ምርት ለመሸፈን ታቅዶ ስራው ተጀምሯል ብለዋል።
የኢሉ ገላን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርናና መሬት አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በንቲ በበኩላቸው፣ የወረዳው አርሶ አደሮች የሩዝ ምርት የኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴን እየተላመዱ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

በወረዳው በ2018/19 የምርት ዘመን 5 ሺህ ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት ለመሸፈን ታቅዶ፣ የግብርና ግብዓቶችን ለአርሶ አደሮቹ በማቅረብ ዘር የመዝራት ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።
ከወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ዘውዱ ዘነበ፤ የሩዝ ሰብልን በኩታ ገጠም መዝራት ከጀመሩ አራት ዓመታት እንደሆናቸው ገልጸው፣ ቀደም ሲል ከሄክታር አነስተኛ ምርት ያገኙ እንደነበር አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ግን በግብርና ባለሙያዎች በሚደረግላቸው ሙያዊ ድጋፍ ታግዘው ከአንድ ሄክታር ማሳቸው እስከ 80 ኩንታል የሩዝ ምርት ለማግኘት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026