🔇Unmute
አሶሳ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ አሶሳ ዩኒቨርስቲ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች በክህሎት የታነፀ ትውልድ ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
ዩኒቨርስቲው በ13ኛ ዙር በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሃግብር ያስተማራቸውን 673 ተማሪዎች አስመርቋል።

የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ያሬድ ሙሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርስቲው በተግባር ተኮር ሳይንስ ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የምርምር ስራዎችን በማከናወን አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ነው።
በተለይም በግብርና፣ እና በማዕድን ዘርፍ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታነፀ እና በክህሎት የበለፀገ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀዋል።
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች ሀገሪቱ ለምትፈልገው የተማረ የሰው ሀይል ተጨማሪ አቅም ይሆናሉ ብለዋል።

ተመራቂዎች ለኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የብልጽግና ጉዞ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም ነው ያሳሰቡት።
በመርሃ ግብሩ ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስትር የባህልና ቋንቋ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...
Jun 17, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...
Jun 17, 2026
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026