የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ላይ በትኩረት እየሰራ ነው

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ አሶሳ ዩኒቨርስቲ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና ማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች በክህሎት የታነፀ ትውልድ ለማፍራት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርስቲው በ13ኛ ዙር በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሃግብር ያስተማራቸውን 673 ተማሪዎች አስመርቋል።


የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ያሬድ ሙሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርስቲው በተግባር ተኮር ሳይንስ ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የምርምር ስራዎችን በማከናወን አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ነው።

በተለይም በግብርና፣ እና በማዕድን ዘርፍ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በማውጣት የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንዲሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታነፀ እና በክህሎት የበለፀገ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልፀዋል።

በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ ተመራቂዎች ሀገሪቱ ለምትፈልገው የተማረ የሰው ሀይል ተጨማሪ አቅም ይሆናሉ ብለዋል።


ተመራቂዎች ለኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የብልጽግና ጉዞ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚገባቸውም ነው ያሳሰቡት።

በመርሃ ግብሩ ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስትር የባህልና ቋንቋ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026