የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ተቋማት የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በተጨባጭ እየመለሱ ነው

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፣ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፡– በኦሮሚያ ክልል እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች በተጨባጭ እየመለሱ መሆናቸውን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ ገለፁ።


የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጠው የ'አዳማ ሲቲ አሬና' ወይም የህዝብ አደባባይ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።


ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው ይኸው ሁለገብ ማዕከል የህዝባዊ ኩነቶችና ዝግጅቶች ማስተናገጃ ስፍራ፣ ዘመናዊ የዳታ ማዕከል፣ ቤተ-መጻሕፍት እና የካፌቴሪያ አገልግሎቶች፣ የገበያ ማዕከልና የስፖርት መዘውተሪያ ስፍራዎች፣ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ ያለው መሆኑ ተመልክቷል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ በርካታ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት በቅተዋል።

በመጠናቀቅ ላይ ባለው በዚህ በጀት ዓመት ብቻ ከ28 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች በሁለት ምዕራፎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ጠቁመዋል።

ዛሬ የተመረቀው የአዳማ ከተማ የህዝብ አደባባይ የ'ስማርት አዳማ' ግቦችን ለማሳካት ከማገዙ ባለፈ፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በመልካም አስተዳደር ረገድ የሚታዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ይረዳል ብለዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት በተጨባጭ ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ስራ አጥነትና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።

የክልሉ ነዋሪም በየአካባቢው ለተገነቡ ፕሮጀክቶች ተገቢው ክትትልና እንክብካቤ ሊያደርግላቸው እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴ በበኩላቸው፣ የልማት ፕሮጀክቶቹ ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር ያረጋገጥንባቸውና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ ናቸው ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸውንም ገልጸዋል።


ከተማዋን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግና ስራ አጥነትን ለመቀነስ በተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የኮሪደር ልማት ስራዎች መሳካታቸውን፣ የመንግስት አገልግሎትና የሀብት አስተዳደር ሥርዓት መዘመኑን፣ የመሬት ሀብት አስተዳደር ከውስብስብ ችግሮች ወጥቶ ለልማት አጋዥ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ይህ የአሰራር ማዘመን ሂደት የከተማዋን ገቢ ከማሳደጉም በላይ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ትልቅ አቅም መፍጠሩን አቶ ኃይሉ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026