የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ እመርታ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማስፋት ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ ነው - የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

Jun 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሰኔ 22/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ እመርታ የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማስፋት ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለጸ።

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫ በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ዘርፎች የሀገርን ዕድገት የሚያፋጥን አቅም እየፈጠሩ ይገኛል።

የብዝኅ ኢኮኖሚ የልማት አቅጣጫ እመርታዊ ውጤትም ምርታማነትን በማሻሻል፣ ንግድና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አስቻይ ሁኔታን ፈጥሯል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በከተማና ገጠር የተፈጠረው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትም በሁሉም ዘርፍ በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚእንዲሆኑ እያደረገ ነው።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ እንዳሉት፤ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የነበረውን ግብርና መር የኢኮኖሚ ሥርዓት ወደ ብዝኅ ዘርፍ ማሸጋገር አስችሏል።

ይህም የኢትዮጵያን የልማት አማራጮች በማስፋትና የዘርፎችን ምርታማነት በማሳደግ የኢኮኖሚ ዕድገትና ተወዳዳሪነትን የሚያሻሽል አቅም እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በብዝኅ ኢኮኖሚ ሥርዓት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና አይ.ሲ.ቲ. የተፈጠረው እመርታዊ ውጤትም የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማስፋት ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩም ግዙፍ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የዜችን የሥራ ዕድል በማስፋት ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ርዕይ መሰረት እየጣሉ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የከተሞች ኮሪደር፣ የቱሪዝምና የኢትዮጵያ ታምርት ሀገር አቀፍ ንቅናቄም የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የሚሊዮኖች ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት በማስፋት ከኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ዘርፍ የዕድገት አማራጮች ጋር በማጣጣም በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በሚቀጥሉት ሶሰት ዓመታትም በሀገር ውስጥ 16 ሚሊየን ዜጎችን በውጭ ሀገራት ደግሞ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026