የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቱሪዝም መሰረተ ልማት ግንባታ የሀገሪቱን ስነ ምህዳርና ዘላቂ ልማትን ባገናዘበ መልኩ እየተከናወነ ነው -  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡-የቱሪዝም መሰረተ ልማት ግንባታ የሀገሪቱን ስነ ምህዳርና ዘላቂ ልማት ባገናዘበ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ቱሪዝም-አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር" በሚል ከኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የቱሪዝም መሰረተ ልማት ስነ-ምህዳርን፣ ዘላቂ ቱሪዝምን እና አረንጓዴ ልማትን ባካተተ መልኩ እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የቱሪዝም ዘርፍ ማነቆዎችን ለመፍታት መሰረተ ልማት በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፍሎ በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል፡፡

በዚህም የመዳረሻ ስፍራዎች ልማት፣ የቱሪስቶች ማረፊያ ቦታዎች፣ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እንዲሁም የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ሰባት ተጨማሪ ኤርፖርቶች ተመርቀው ስራ የጀመሩ ሲሆን፤ ቀሪዎቹም በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ብለዋል።

ባለፉት ስድስትና ሰባት ዓመታት የተከናወኑት የገበታ ፕሮጀክቶች በሀገሪቱ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ማሳረፍ መቻላቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በገበታ ለሀገርና ለትውልድ የአርባምንጭ እና የጅማ ፕሮጀክቶች ከሞላ ጎደል ያለቁ ሲሆን፤ የአርባ ምንጭ ፕሮጀክት በቅርቡ ይመረቃል ብለዋል።

የኮሪደር ልማትና የሪዞርቶች ተፅዕኖን ሲገልጹም በአርባ ምንጭ፣ በጎርጎራ፣ በሀይቅ፣ በጅማ እና በጅጅጋ (ሸበሌ) የተገነቡት ሪዞርቶችና የኮሪደር ልማቶች የአካባቢውን ከተሞች ገጽታ በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ተጨባጭ ተፅዕኖ እያመጡ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት የተጠቀሟቸው የኢንቨስትመንት ምንጮች እጅግ የተለያዩ ሲሆኑ በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

እነኚህም የመንግስትና የግል አጋርነት፣ የሕዝብ ተሳትፎ እንዲሁም የወዳጅ ሀገራት ድጋፍ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

አሁን ላይ እየታየ ያለው የቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃት የዜጎች፣ የግሉ ዘርፍ፣ የውጭ ወዳጅ ሀገራት እና የግለሰቦች የሀብት፣ የሀሳብና የእውቀት ድምር ውጤት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቡናን በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

አዳማ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ቡናን ከመደበኛ ወቅት በተጨማሪ በበጋ መስኖ በማልማት የአምራቹን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መደ...

Jun 17, 2026

 በቀጣዮቹ 90 ቀናት የመዲናዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሠራል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣዮቹ 90 ቀናት የከተማዋን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላ...

Jun 17, 2026

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026