የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቱሪዝም መሰረተ ልማት ግንባታ የሀገሪቱን ስነ ምህዳርና ዘላቂ ልማትን ባገናዘበ መልኩ እየተከናወነ ነው -  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Jul 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡-የቱሪዝም መሰረተ ልማት ግንባታ የሀገሪቱን ስነ ምህዳርና ዘላቂ ልማት ባገናዘበ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ቱሪዝም-አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር" በሚል ከኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የቱሪዝም መሰረተ ልማት ስነ-ምህዳርን፣ ዘላቂ ቱሪዝምን እና አረንጓዴ ልማትን ባካተተ መልኩ እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የቱሪዝም ዘርፍ ማነቆዎችን ለመፍታት መሰረተ ልማት በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፍሎ በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል፡፡

በዚህም የመዳረሻ ስፍራዎች ልማት፣ የቱሪስቶች ማረፊያ ቦታዎች፣ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እንዲሁም የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ሰባት ተጨማሪ ኤርፖርቶች ተመርቀው ስራ የጀመሩ ሲሆን፤ ቀሪዎቹም በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ብለዋል።

ባለፉት ስድስትና ሰባት ዓመታት የተከናወኑት የገበታ ፕሮጀክቶች በሀገሪቱ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ማሳረፍ መቻላቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በገበታ ለሀገርና ለትውልድ የአርባምንጭ እና የጅማ ፕሮጀክቶች ከሞላ ጎደል ያለቁ ሲሆን፤ የአርባ ምንጭ ፕሮጀክት በቅርቡ ይመረቃል ብለዋል።

የኮሪደር ልማትና የሪዞርቶች ተፅዕኖን ሲገልጹም በአርባ ምንጭ፣ በጎርጎራ፣ በሀይቅ፣ በጅማ እና በጅጅጋ (ሸበሌ) የተገነቡት ሪዞርቶችና የኮሪደር ልማቶች የአካባቢውን ከተሞች ገጽታ በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ተጨባጭ ተፅዕኖ እያመጡ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት የተጠቀሟቸው የኢንቨስትመንት ምንጮች እጅግ የተለያዩ ሲሆኑ በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

እነኚህም የመንግስትና የግል አጋርነት፣ የሕዝብ ተሳትፎ እንዲሁም የወዳጅ ሀገራት ድጋፍ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

አሁን ላይ እየታየ ያለው የቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃት የዜጎች፣ የግሉ ዘርፍ፣ የውጭ ወዳጅ ሀገራት እና የግለሰቦች የሀብት፣ የሀሳብና የእውቀት ድምር ውጤት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026