🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2018 (ኢዜአ)፡-የቱሪዝም መሰረተ ልማት ግንባታ የሀገሪቱን ስነ ምህዳርና ዘላቂ ልማት ባገናዘበ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ቱሪዝም-አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር" በሚል ከኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የቱሪዝም መሰረተ ልማት ስነ-ምህዳርን፣ ዘላቂ ቱሪዝምን እና አረንጓዴ ልማትን ባካተተ መልኩ እየተገነባ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የቱሪዝም ዘርፍ ማነቆዎችን ለመፍታት መሰረተ ልማት በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፍሎ በትኩረት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል፡፡
በዚህም የመዳረሻ ስፍራዎች ልማት፣ የቱሪስቶች ማረፊያ ቦታዎች፣ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እንዲሁም የዲጂታል መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ሰባት ተጨማሪ ኤርፖርቶች ተመርቀው ስራ የጀመሩ ሲሆን፤ ቀሪዎቹም በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ብለዋል።
ባለፉት ስድስትና ሰባት ዓመታት የተከናወኑት የገበታ ፕሮጀክቶች በሀገሪቱ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ማሳረፍ መቻላቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በገበታ ለሀገርና ለትውልድ የአርባምንጭ እና የጅማ ፕሮጀክቶች ከሞላ ጎደል ያለቁ ሲሆን፤ የአርባ ምንጭ ፕሮጀክት በቅርቡ ይመረቃል ብለዋል።
የኮሪደር ልማትና የሪዞርቶች ተፅዕኖን ሲገልጹም በአርባ ምንጭ፣ በጎርጎራ፣ በሀይቅ፣ በጅማ እና በጅጅጋ (ሸበሌ) የተገነቡት ሪዞርቶችና የኮሪደር ልማቶች የአካባቢውን ከተሞች ገጽታ በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ተጨባጭ ተፅዕኖ እያመጡ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡
የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት የተጠቀሟቸው የኢንቨስትመንት ምንጮች እጅግ የተለያዩ ሲሆኑ በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
እነኚህም የመንግስትና የግል አጋርነት፣ የሕዝብ ተሳትፎ እንዲሁም የወዳጅ ሀገራት ድጋፍ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
አሁን ላይ እየታየ ያለው የቱሪዝም ዘርፍ መነቃቃት የዜጎች፣ የግሉ ዘርፍ፣ የውጭ ወዳጅ ሀገራት እና የግለሰቦች የሀብት፣ የሀሳብና የእውቀት ድምር ውጤት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026