የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ይገባል

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡-የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት" በሚል መሪቃል በጅማ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።


የሳይበር ደህንነት ወርን በማስመልከት በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን መድረኩም ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማ እንዳለው ተመላክቷል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎትን ለማስፋፋት ትኩረት ከመስጠት ባለፈ በሳይበር ደህንነት ላይ ጠንካራ ሥራ እየተሰራ ነው።

ተቋማቱም የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ አስተማማኝ እና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ትኩረት መሰጠቱን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።

የዲጂታላይዜሽን አገልግሎት ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሁልግዜም ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሳይበር ደህንነትን ወርም ይህን እውን ለማድረግና የሀሰተኛ የመረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር በማለም እንደሚከበር አክለዋል።

በተለይም የስማርት ከተማን በመገንባት ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ የዲጂታል አገልግሎት ጉልህ አስተዋጾ እንዳለው ነው የገለጹት።

ለተግባራዊነቱም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከርና የስማርት ከተሞችን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የጅማ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዋሴ ግርማ በበኩላቸው እንዳሉት በጅማ ከተማ ዲጂታል አገልግሎቶችን በመተግበር ስማርት ከተማ ለመገንባት እየተሰራ ነው።

ለእዚህም ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በከተማዋ ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመድረኩ የተለያዩ ተቋማት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026