የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት በሥራ ዕድልና በቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠቃሚ አድርጎናል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ሚያዝያ 27/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት፤ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ክህሎታቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው የእድሉ ተጠቃሚዎች ገለጹ።

የሐረሪ ክልል በታሪኩና በቱሪስት መስህብነቱ ቢታወቅም፣ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የክልሉን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።

በተለይም መንግስት የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሬን ለማዳን የጀመረው "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ በክልሉ ውጤት ማምጣት ጀምሯል።

ክልሉ ለኢንቨስትመንት አመቺ የሆኑ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን በማጠናከር፣ አዳዲስ ፋብሪካዎች ወደ ሥራ እንዲገቡና ነባሮቹ ደግሞ በሙሉ አቅማቸው እንዲያመርቱ እያደረገ ያለው ጥረት ለዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ፣ የኢንዱስትሪ ባህልና የቴክኖሎጂ ዕውቀት በአካባቢው እንዲሰርጽ እያደረገ ይገኛል።


ወጣት ፈርሃን ተውፊቅ የሐረር ከተማ ተወላጅ ሲሆን በከተማው ኢንዱስትሪ ዞን በሚገኘው ማስ ኢንጅነሪንግ ኢንተርፕራይዝ በተለያዩ የሙያ ዘርፍ እርሱና ሌሎች ጓደኞቹ የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተናግሯል።

በክልሉ የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት የተሻለ የቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲያገኙ ከማስቻሉ ባለፈ ከውጭ የሚመጡ ምርቶችን በኢንተርፕራይዙ በማምረት የውጭ ምንዛሬን የማስቀረት ተግባር እያከናወኑ መሆኑን አስረድቷል።

በከተማው በብረታብረት ዘርፍ ወደ ስራ በመግባት ከኢንዳስትሪው ባገኙት የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ነስረዲን አህመድ ናቸው።

በተለይም የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ለከተማዋ የኮሪደር ልማት የሚውሉ የፖል ብረት ምርቶች በስፋት እንዲቀርቡና ከተማዋን እንዲያስውቡ ማድረጉን አቶ ነስረዲን ገልጸዋል።

በዱቄት ፋብሪካ የስራ ዕድል ተጠቃሚ በመሆኗ እራሷንና ቤተሰቧን እያገዘች መሆኑን የገለጸችው ደግሞ ወጣት ኤደን ፍሰሃ ናት።

በሐረር የኢንዱስትሪዎች መነቃቃት ለስራ ፈላጊውም ጭምር አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን ተናግራለች።

ከዚህ ባለፈም ልምድ፣ ተሞክሮና የተሻሻሉ አሰራሮችን እየቀሰሙ እንደሚገኙ የገለጸችው ወጣት ኤደን፣ በዚህም ለፋብሪካ ባለቤቶች ምስጋና አቅርባለች።


ፋብሪካው 120 ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል ያሉት ደግሞ በከተማው ኢንዱስትሪ ዞን የሚገኘው የቀነኒ ዱቄት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ተስፋ አስፋው ናቸው።

ፋብሪካው በአሁኑ ወቅት ከውጪ ይገባ የነበረውን የስንዴ ዱቄት በአገር ውስጥ በማምረት እና ለአካባቢው በማከፋፈል ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ በቀጣይም የፓስታ፣ መኮሮኒን እና ሌሎች ምርቶችን ለማምረት የዝግጅት ስራ እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የሐረሪ ክልል ኢንተርፕራይዞች ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አቶ ኡስማኢል ዩስፍ በበኩላቸው፤ በክልሉ አዳዲስና ነባር መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ስራ በማስገባት ተኪ ምርቶችን በስፋት የማምረት ተግባር መጠናከሩን ተናግረዋል።


በተለይም የክልሉን ኢኮኖሚ ይበልጥ የሚያጎለብቱና የስራ እድልን የሚያስፋፉ ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ግንባታቸው ተጠናቆ ማሽነሪዎችን የማስገባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026