🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሰራሩን በማዘመን ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ።
ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የበጀት አፈፃፀምንና የ2019 በጀት ዓመት እቅድን ገምግሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አመራሮች እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ላለፉት 85 ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ በጽሑፍም በፎቶ ግራፍም ሰንዶ የያዘ አንጋፋ ተቋም ነው፡፡

በድርጅቱ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኤፍሬም ተክሌ፤ በአሁኑ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ለህትመት ሚዲያው ፈታኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ድርጅቱም የዲጂታል ሚዲያውን መስፋፋት ታሳቢ አድርጎ እዩሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ በህትመትም በዲጂታልም ተወዳዳሪና ተደራሽ ለመሆን ለዲጂታል አሰራሮች ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል፡፡

የድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወንድም ተክሉ በበኩላቸው፤ ድርጅቱ የራሱ የጋዜጣ እና መጽሔት ህትመት ቤት አለመኖሩ ለሥራው ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነበት ተናግረዋል፡፡
ይህ በተደጋጋሚ ሲነሳ የቆየ ችግር መሆኑን አንስተው፤ የጋዜጣና የመፅሔት ህትመት የየራሳቸው ባህሪ፣ ጥራትና ደረጃ የሚጠይቁ በመሆናቸው በተለያዩ ማተሚያ ቤቶች ለማሳተም እንደሚገደድ ጠቁመዋል።
ለሁለቱም ህትመቶች የሚሆኑ ማተሚያ ቤቶች እንዲኖረው ቢደረግ የድርጅቱን አሠራር እንደሚያሻሽልና ወጪን እንደሚቀንስ ጠቅሰዋል።
ከዚህም ባለፈ ለሌሎች ድርጅቶች ጭምር የህትመት አገልግሎት በመስጠት የገቢ ምንጭ ማድረግ እንደሚችልም አንስተዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጄ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ብዝኃነትን መሰረት ያደረገ የህትመት አቅምን ለማሳደግ እያደረገ ያለውን የሪፎም ሥራ አድንቀዋል።
ድርጅቱ ከወቅቱ ጋር ለመዘመንና ተወዳዳሪ ለመሆን እያደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል።
የድርጅቱ ማተሚያ ቤት ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ምክክር እንደሚደረግበትና እንደሚታይ ጠቁመዋል።
ተቋሙ አሠራሩን ለማሻሻልና የገቢ አቅሙን ለማሳደግ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #ENA
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026