የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ ሀገራዊ ክብርና ሉአላዊነትን የማረጋገጥ ወሳኝ ሀገራዊ አጀንዳ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ አጀንዳ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በወቅቱ፤ የኢትዮጵያ ክብርና ሉአላዊነት በፅኑ መሰረት ላይ ማኖር የሚቻለው በምግብ ራስን በመቻል ከተረጅነት መውጣት ሲቻል መሆኑን ገልጸው ከተረጅነት የመውጣት ጥረት የብሄራዊ ጥቅምና የሉአላዊነት ጉዳይ ነው ብለዋል።

ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ ይገኛል ነው ያሉት።

በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ የመቀየር ጉዳይ በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።

የሀገርን እምቅ ሃብቶች በማልማት የምርት አቅምን በማሳደግ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን በራስ አቅም የመመከት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት አስጠብቆ ለመዝለቅ የተረጅነትና የልመና አስተሳሰብን በማስወገድ አልምቶና አምርቶ ብልጽግናዋን እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የቤተሰብና የማህበረሰብ ብልፅግና ማረጋገጥና ሀገርን ከተረጅነትና ጥገኝነት ማላቀቅ የመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫ ግቦች መካከል መሆኑንም ለአብነት ጠቅሰዋል።

ከድህነት በመውጣት የሚደረገውን ጥረትና እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን አንስተው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር ) በበኩላቸው፤ የሀገርን እምቅ ጸጋዎች በማልማት ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ የተሻገረ ስኬት ማስመዝገብ እንደሚቻል የተመዘገቡ ውጤቶች ማሳያ ናቸው ብለዋል።


በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ባለፉት ጥቂት አመታት የመጡ ለውጦችና የተመዘገቡ ስኬቶች እምቅ አቅሞችን ወደ ተጨባጭ ውጤት መለወጥ ያስቻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በግብርናው ዘርፍ በተለያዩ ኢንሸቲቮች የተጀመሩ የልማት ጥረቶችን ዘላቂ በማድረግ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር የሀገር ወሳኝ አጀንዳ መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያን ተረጂነት ታሪክ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።


በተረጅነት ዙሪያ የዜጎች የአስተሳሰብ ለውጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ሚዲያዎች የይዘት ስራዎችን በልዩ ትኩረት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026