የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ ሀገራዊ ክብርና ሉአላዊነትን የማረጋገጥ ወሳኝ ሀገራዊ አጀንዳ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት የማረጋገጥ ወሳኝ አጀንዳ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና በግብርና ሚኒስቴር ትብብር "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" በሚል መሪ ሃሳብ በሐዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) በወቅቱ፤ የኢትዮጵያ ክብርና ሉአላዊነት በፅኑ መሰረት ላይ ማኖር የሚቻለው በምግብ ራስን በመቻል ከተረጅነት መውጣት ሲቻል መሆኑን ገልጸው ከተረጅነት የመውጣት ጥረት የብሄራዊ ጥቅምና የሉአላዊነት ጉዳይ ነው ብለዋል።

ከተረጂነት የመውጣት ጉዳይ የብሔራዊ ጥቅም አካል ሆኖ የመንግስት ስትራቴጂክ አጀንዳ ተደርጎ በፖሊሲ አቅጣጫ እየተመራ ይገኛል ነው ያሉት።

በመሆኑም ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ብልጽግና እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የድህነት ታሪክ የመቀየር ጉዳይ በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ይገኛል ብለዋል።

የሀገርን እምቅ ሃብቶች በማልማት የምርት አቅምን በማሳደግ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን በራስ አቅም የመመከት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን ክብርና ሉአላዊነት አስጠብቆ ለመዝለቅ የተረጅነትና የልመና አስተሳሰብን በማስወገድ አልምቶና አምርቶ ብልጽግናዋን እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የቤተሰብና የማህበረሰብ ብልፅግና ማረጋገጥና ሀገርን ከተረጅነትና ጥገኝነት ማላቀቅ የመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫ ግቦች መካከል መሆኑንም ለአብነት ጠቅሰዋል።

ከድህነት በመውጣት የሚደረገውን ጥረትና እንደ ሀገር የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን አንስተው በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር ) በበኩላቸው፤ የሀገርን እምቅ ጸጋዎች በማልማት ምርታማነትን በማሳደግ ከራስ የተሻገረ ስኬት ማስመዝገብ እንደሚቻል የተመዘገቡ ውጤቶች ማሳያ ናቸው ብለዋል።


በተለያዩ የሀገሪቷ አካባቢዎች ባለፉት ጥቂት አመታት የመጡ ለውጦችና የተመዘገቡ ስኬቶች እምቅ አቅሞችን ወደ ተጨባጭ ውጤት መለወጥ ያስቻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም በግብርናው ዘርፍ በተለያዩ ኢንሸቲቮች የተጀመሩ የልማት ጥረቶችን ዘላቂ በማድረግ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር የሀገር ወሳኝ አጀንዳ መሆኑን አንስተው የኢትዮጵያን ተረጂነት ታሪክ የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።


በተረጅነት ዙሪያ የዜጎች የአስተሳሰብ ለውጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተው በዚህ ረገድ ሚዲያዎች የይዘት ስራዎችን በልዩ ትኩረት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026