የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በዞኑ የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እየተጠናቀቁ ነው

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጭሮ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሐረርጌ ዞን የሕብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚያቃልሉ የልማት ፕሮጀክቶች በፍጥነት እየተጠናቀቁ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ ገለጹ።

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ እና ሐዊ ጉዲና ወረዳዎች 950 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ተቋማት በክልልና በዞን ከፍተኛ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች ተመርቀዋል።


በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ዋና አስተዳዳሪዋ ወይዘሮ ኢክራም ጠሀ እንዳሉት፤ መንግሥት ለሕዝብ የገባውን ቃል ወደ ተግባር በመለወጥ ሕብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት እየሠራ ይገኛል።

የልማት ተቋማቱን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ የሕብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄዎች ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።


ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል በሐዊ ጉዲና የአርብቶ አደር ወረዳ ከ890 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የንጹሕ ውኃ ተቋም አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ከ40 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች አገልግሎት የሚሰጥና የአርብቶ አደሩን እንስሳት የውኃ አቅርቦት ፍላጎት የሚያሟላ በመሆኑ፣ የዘመናት ጥያቄን መመለስ የቻለ መሆኑንም ተናግረዋል።

ሌላው በጭሮ ወረዳ የተገነባው የመረዋ ድልድይ የአካባቢውን አርሶ አደሮች የትራንስፖርትና የቁልፍ መገናኛ ችግር ለመፍታት ታስቦ ግንባታው መከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በምረቃው ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል መሬት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አሰፋ በበኩላቸው፤ መንግሥት የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት በማሟላት ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሠራቸው ሥራዎች እጅግ ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይም የሕብረተሰቡን ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ከመመለስ ባለፈ፣ ለልማት ፕሮጀክቶች ፍጥነትና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አመልክተዋል።

የዞኑ አስተዳደርም የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች በየደረጃውና በፍጥነት ለመመለስ የሚያደርገውን የተቀናጀ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026