የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራ ልዑክ በአዘርባጃን የተቀናጀ የከተማ ልማት ፕሮጀክትን ጎበኘ

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ግንቦት 12 /2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራ የልዑካን ቡድን በአዘርባጃን ያለውን የተቀናጀ የከተማ ልማት ፕሮጀክት ጎብኝቷል።

ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ አዘርባጃን በአሁኑ ወቅት ካስመዘገበችው ከፍተኛ ዕድገት ጎን ለጎን የከተማ መልሶ ማልማት ሥራዎችን አጠናክራ መቀጠሏን ገልጸዋል።

አሮጌ መንደሮችን በማንሳት የማደስ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ጥቅም ላይ ያልዋሉ ቦታዎችን ለይቶ የማልማት ስትራቴጂ እየተከተለች እንደሚገኝ አመልክተዋል።

በዚህም በ16 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቁ 50 ሺህ መኖሪያ ቤቶች፣ ሆቴሎችና ተያያዥ የልማት ሥራዎች በ"Sea Breeze ፕሮጀክት" ሥር በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙና የግሉ ዘርፍም ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት በከፍተኛ ደረጃ እየተሳተፈ መሆኑንም ነው ያነሱት።

በአዲስ አበባም፣ በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን እና ተያያዥ ልማቶችን ለመገንባት ታቅዶ በከፍተኛ ርብርብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።


ከተማ አስተዳደሩ ያረጁና የተጎሳቀሉ አካባቢዎችን የመቀየርና የማደስ ሥራዎችን እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ቀደም ሲል በአግባቡ ጥቅም ላይ ያልዋሉ እንደ የጫካ ፕሮጀክት፣ ገላን-ጉራ፣ መሐመድያ መንደር እና አዲስ ቱሞሮ ያሉ አካባቢዎችን በመጠቀም አዲስ ከተማ የመገንባት ያህል ምቹ የልማትና የመኖሪያ ስፍራዎችን ለመፍጠር እየተሠራ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ይህ መጠነ-ሰፊ የቤት ልማትና የከተማ ማደስ እንቅስቃሴ በዋናነት የመኖሪያ ቤት ችግርን ለማቃለልና መዲናዋን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የታለመ ነው ብለዋል ከንቲባዋ።

በቀጣይነትም በላቀ ጥረትና በልማት ልኅቀት አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ በማድረግ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ግንባር-ቀደም ለማድረግ አበክሮ የመሥራት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026