🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ግንቦት 12 /2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራ የልዑካን ቡድን በአዘርባጃን ያለውን የተቀናጀ የከተማ ልማት ፕሮጀክት ጎብኝቷል።
ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፤ አዘርባጃን በአሁኑ ወቅት ካስመዘገበችው ከፍተኛ ዕድገት ጎን ለጎን የከተማ መልሶ ማልማት ሥራዎችን አጠናክራ መቀጠሏን ገልጸዋል።
አሮጌ መንደሮችን በማንሳት የማደስ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ጥቅም ላይ ያልዋሉ ቦታዎችን ለይቶ የማልማት ስትራቴጂ እየተከተለች እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በዚህም በ16 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቁ 50 ሺህ መኖሪያ ቤቶች፣ ሆቴሎችና ተያያዥ የልማት ሥራዎች በ"Sea Breeze ፕሮጀክት" ሥር በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙና የግሉ ዘርፍም ከመንግሥት ጋር በመቀናጀት በከፍተኛ ደረጃ እየተሳተፈ መሆኑንም ነው ያነሱት።
በአዲስ አበባም፣ በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን እና ተያያዥ ልማቶችን ለመገንባት ታቅዶ በከፍተኛ ርብርብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ያረጁና የተጎሳቀሉ አካባቢዎችን የመቀየርና የማደስ ሥራዎችን እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ቀደም ሲል በአግባቡ ጥቅም ላይ ያልዋሉ እንደ የጫካ ፕሮጀክት፣ ገላን-ጉራ፣ መሐመድያ መንደር እና አዲስ ቱሞሮ ያሉ አካባቢዎችን በመጠቀም አዲስ ከተማ የመገንባት ያህል ምቹ የልማትና የመኖሪያ ስፍራዎችን ለመፍጠር እየተሠራ መሆኑን በማሳያነት ጠቅሰዋል።
ይህ መጠነ-ሰፊ የቤት ልማትና የከተማ ማደስ እንቅስቃሴ በዋናነት የመኖሪያ ቤት ችግርን ለማቃለልና መዲናዋን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ የታለመ ነው ብለዋል ከንቲባዋ።
በቀጣይነትም በላቀ ጥረትና በልማት ልኅቀት አዲስ አበባን እንደ ስሟ አበባ በማድረግ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ግንባር-ቀደም ለማድረግ አበክሮ የመሥራት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026