የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ በልማታዊ ሴፍትኔትና ምግብ ዋስትና የታቀፉ ወገኖች ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ ነው

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ231 ሺህ በላይ ወገኖች በከተማ ሴፍትኔትና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ታቅፈው ሃብት በማፍራት ላይ መሆናቸውን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ገለፀ።

የቢሮ ኃላፊው ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በከተሞች የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትብብር እየተከናወኑ ይገኛል።

በዚህም ከ195 ሺህ በላይ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ወገኖች በከተሞች በሚከናወኑ የልማት ስራዎች በማሳተፍ የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥም ባለፈ በዘላቂነት ሃብት እንዲያፈሩ እየተደረገ ይገኛል።

ተጠቃሚዎቹ በ18 ከተሞች በአረንጓዴ እና በተፋሰስ ልማት፣ በከተማ ፅዳትና ውበት፣ በማህበራዊ ተቋማት ግንባታና መሰል የልማት ስራዎች እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ተጠቃሚዎቹ በተሰማሩበት መስክ በየወሩ ከሚያገኙት ክፍያ በተጨማሪም ከፕሮግራሙ ሲመረቁ በዘላቂነት በገቢ ማስገኛ ስራዎች እንዲሳተፉ እየተደረገ ነው ።

በተለይም በሰብል ልማት፣ በቁም እንስሳት ማድለብ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳ ውጤቶች ስራና መሰል ዘርፎች እንዲሳተፉ በማድረግ ሃብት እንዲያፈሩ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በተጨማሪም ከ36 ሺህ በላይ አቅመ ደካሞች፣ የጤና ችግር ያለባቸውና ደጋፊ የሌላቸው ወገኖች በቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ እየተደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።

በተያዘው ዓመትም በፕሮግራሙ ታቅፈው ድጋፍ ሲደረግላቸው የቆዩና ተጨባጭ ለውጥ ያስመዘገቡ 18 ሺህ ተጠቃሚዎች ከፕሮግራሙ መመረቃቸውን አረጋግጠዋል።

ፕሮግራሙ የበርካታ ወገኖችን ኑሮ ከማሻሻሉም በላይ በከተሞች የሚከናወነውን ልማት እንዲፋጠን የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሆነም አብራርተዋል።

የፕሮግራሙ ውጤታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ለፕሮግራሙ ማስፈፀሚያ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት እየተተገበረ ሲሆን 39 ሺህ ወገኖች ከፕሮግራሙ ማስመረቅ እንደተቻለ ሃላፊው ጨምረው አስታውቀዋል።

በባህር ዳር ከተማ በፕሮግራሙ ታቅፈው ተጠቃሚ የሆኑት ወይዘሮ አስናቀች ደምለው እንዳሉት፤በፕሮግራሙ ተሳታፊ በመሆን በጀመሩት ቁጠባና የመቋቋሚያ ገንዘብ አሁን ላይ በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ተሰማርተው እየሰሩ ይገኛል።

ቀደም ሲል ኑሯቸው ከእጅ ወደ አፍ እንደነበረ አስታውሰው፤ አሁን ላይ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን በአግባቡ ከማስተዳደር ባለፈ ሃብት በማፍራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በፕሮግራሙ ለሦስት ዓመታት በልማት ስራ ሲሳተፉ የቆየቱ ወይዘሮ ኤልሳ አሻግሬ ባስመዘገቡት ውጤት ተመርቀው በራሳቸው የንግድ ስራ ላይ መሰማራታቸውን ይገልፃሉ፡፡

አሁኑ ወቅትም በተደረገላቸው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ሃብት ለማፍራት መቻላቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026