🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ ከተረጅነት ወደ ምርታማነት በሚል መሪ ሐሳብ የውይይት መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ መድረክ በምርታማነት ጉዳይ ቁጭት ፈጥሮ የሚተጋ ማህበረሰብ መገንባትን ያለመ ነው።
ከዚህ ቀደም በአዳማ እና በሃዋሳ በተዘጋጁ ተመሳሳይ መድረኮች የየክልሉን ተሞክሮ የዳሰሱ ውይይቶች ተካሂደዋል።
የተለያዩ ክልሎችም ከተረጅነት ወደ ምርታማነትና ወደ ሉዓላዊ ክብር ለመጓዝ እያከናወኗቸው ያሉ ተግባራት ተዳሰዋል።

በዛሬው መድረክ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ሮዛ ዑመር፣ በድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ ተገኝተዋል።
እንዲሁም የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ከድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር፣ ከሶማሌ፣ ከሐረሪ እና ከአፋር ክልሎች የተውጣጡ አርሶ አደሮች በመድረኩ እየተሳፉ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026