🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ)፦ ከተረጅነት ወደ ምርታማነት በሚል መሪ ሐሳብ የውይይት መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ መድረክ በምርታማነት ጉዳይ ቁጭት ፈጥሮ የሚተጋ ማህበረሰብ መገንባትን ያለመ ነው።
ከዚህ ቀደም በአዳማ እና በሃዋሳ በተዘጋጁ ተመሳሳይ መድረኮች የየክልሉን ተሞክሮ የዳሰሱ ውይይቶች ተካሂደዋል።
የተለያዩ ክልሎችም ከተረጅነት ወደ ምርታማነትና ወደ ሉዓላዊ ክብር ለመጓዝ እያከናወኗቸው ያሉ ተግባራት ተዳሰዋል።

በዛሬው መድረክ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ፣ የሐረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ሮዛ ዑመር፣ በድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት ዋና ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ ተገኝተዋል።
እንዲሁም የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችም ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ከድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር፣ ከሶማሌ፣ ከሐረሪ እና ከአፋር ክልሎች የተውጣጡ አርሶ አደሮች በመድረኩ እየተሳፉ ይገኛሉ።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026