የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ባለፉት ስድስት ወራት ከጨረታና ከቅጣት 135 ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል -ባለስልጣኑ</p>

Jan 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ጥር 9/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ወራት ህገ-ወጥ እና አዋኪ ድርጊቶችን በመከላከል በተሰሩ ሥራዎች ከጨረታና ከቅጣት ከ 135 ሚሊዮን ብር መገኘቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

ባለሥልጣኑ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸሙን አስመልክቶ በየደረጃው ካሉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርጓል።

በመድረኩ ከመዲናዋ 11 ዱ ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፥ባለስልጣኑ ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ የደንብ ጥሰቶችን ጨምሮ አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከል ሲሰራ ቆይቷል።

በዚህም በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተገኝተው የተወረሱ ንብረቶችን በጨረታ በመሸጥ 12 ሚሊየን ብር እንዲሁም ህግ በተላለፉ አካላት ላይ ከተጣለ ቅጣት 123 ሚሊየን ብር በአጠቃላይ 135 ሚሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡

በተለይም ህገ-ወጥ ግንባታዎችና የጐዳና ላይ ንግድ እንዲሁም አዋኪ ድርጊቶችና ሌሎች ደንብ መተላለፎችን በመከላከል በርካታ ሥራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል።

በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎች የደንብ መተላለፍን ለመቀነስና ለመከላከል ከፍተኛ አበርክቶ እንደነበራቸው ተናግረዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ባለፉት ስድስት ወራት የተቋም ግንባታ፣የሥልጠናና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት መስራቱን ጠቅሰዋል፡፡

በመዲናዋ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ስራዎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ እና ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲጠቀምባቸው ሰፊ የጥበቃ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ በመዲናዋ የተሰሩ መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ ለመጠበቅና ህግ የሚተላለፉ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ ከባለስልጣኑ ጎን በመቆም እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

በዚህም የደንብ መተላለፎችን በመከላከል የህግ የበላይነትን የሚያረጋግጡ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026