የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

Jun 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ።

ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በየካ ክፍለ ከተማ የተገነባውን 9ኛ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ በዚሁ ወቅት፤ የማዕከሉ መገንባት ህብረተሰቡ ፈጣን፣ ግልጽ እና ፍትሐዊ አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ቀደም ሲል ከህዝብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች የአገልግሎት አሰጣጥ ውስንነት የህዝብ እንግልትና ምሬት ምንጭ መሆናቸውን ማረጋገጥ መቻሉን አውስተዋል።

ለህዝብ ጥያቄ ቅድሚያ መስጠት ዋና መገለጫ የሆነው ከተማ አስተዳደሩ፤ ጥራት ላለው የመንግሥት አገልግሎት እንቅፋት የሆኑ ምክንያቶችን ነቀሶ በማውጣት እልባት እየሰጠ መምጣቱን ተናግረዋል።

በዚህም አልፎ አልፎ ይስተዋሉ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዋል።


በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ የዛሬውን ጨምሮ ዘጠኝ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በማደራጀት ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰዋል።

እነዚህ ማዕከላት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙላቸው እና የበቃ የሰው ሀይል የተሟሉላቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።

የማዕከላቱ ወደ ስራ መግባት ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበትን አሰራርን እውን በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ይነሱ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን መቅረፍ ማስቻላቸውን ነው የተናገሩት።

በቀጣይም በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ጀማሉ ጀንበር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዜጎችን ከእንግልትና ከአላስፈላጊ የገንዘብ ወጭ ታድጓል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026