የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ያደርጋል-የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ልማት ባንክ የሌማት ትሩፋት አካል ለሆነው የኢትዮጵያ የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት የ50 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑን የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና ገለጹ።


ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ ዛሬ በስፔን ሲቪያ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።


በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን ኢትዮጵያን ወክሎ በኮንፍረንሱ ላይ እየተሳተፈ ነው።


“Global Alliance Against Poverty and Hunger” ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን ያዘጋጀው ስብሰባ ተካሄዷል።


የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሌማት ትሩፋት ዙሪያ ያላት ልምድ እንደ ተምሳሌታዊ ፕሮጀክት በስብሰባው ላይ አቅርበዋል።


በተጨማሪ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርጋቸውን ሌሎች ሰፋፊ ጥረቶች አስመልክቶ ያላትን ተሞክሮም አጋርተዋል።


ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።


ኢኒሼቲቩ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ሀገር በቀል ሀሳቦችን እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክተዋል።


በመንግስት እና በህዝቡ በባለቤትነት የተያዘ መሆኑ፣ድህነትን በመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አንጻር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ተናግረዋል።


በተጨማሪም ኢኒሼቲቭ በሀገር ውስጥ ሀብት ላይ በመመስረት የሚተገበር መሆኑን አንስተዋል።


ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ለምታደርጋቸው ትብብሮች ለኢኒሼቲቩ ድጋፍ በማፈላለግ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና ሊኖረው ይችላል ነው ያሉት ሚኒስትሩ።


አክለውም ኢኒሼቲቩን በተጨማሪ ኢንቨስትመንት በስፋት መተግበር እንደሚቻል ገልጸው፥ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ የተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎረም ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል።


በመጨረሻም ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቀነስ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሌሎች ሀገራት መልካም ተሞክሮ ለመማርም ዝግጁ ናት ብለዋል።


የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አዴሲና በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት በሰራችው አመርቂ ስራ በስንዴ ምርት ሙሉ በሙሉ ራሷን መቻሏን ገልጸዋል።


በትኩረት ተገቢው አመራር እና ድጋፍ ከተደረገ በአፍሪካ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደሚቻል የኢትዮጵያ ስኬት እንደ ተጨባጭ ማሳያ ሊወሰድ እንደሚችል አመልክተዋል።


ፕሬዝዳንቱ ባንኩ የኢትዮጵያ የሌማት ትሩፋት አካል የሆነውን የዶሮ እርባታ ፕሮጀክት 50 የሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለመደገፍ መወሰኑን ይፋ አድርገዋል።


ኮንፍረንሱ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።


የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን በሚኖሩ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026