የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአማራ ክልል ከ15 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ምርጥ የሰብል ዘር ለማባዛት ወደ ተግባር ተገባ

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የምርጥ ዘር አቅርቦት እጥረትን ለማቃለል ከ15 ሺህ ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ምርጥ የሰብል ዘር ለማባዛት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

ቀደም ሲል የተባዘው ምርጥ የሰብል ለ2017/2018 የምርት ዘመን ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ እንደሚገኝ ተመልክቷል።

በክልሉ ግብርና ቢሮ የዘር ብዜት ባለሙያ አቶ ጥላዬ ሞገሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የዘር አቅርቦት እጥረት ለማቃለል በምርት ዘመኑ በሁለት የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ በ10 ዩኒየኖችና በ34 የግል ዘር አብዥዎች እየተከናወነ ይገኛል።


እስካሁን በተደረገው የዘር ብዜት እንቅስቃሴም በዕቅድ ከተያዘው መሬት 2 ሺህ 595 ሄክታሩ በበቆሎና ስንዴ ዘር ብዜት መሸፈኑን ተናግረዋል።

ቀሪው መሬት በቀጣይ እንደየዘር ወቅቱ የማባዛት ስራውን በማጠናከር የክልሉን የዘር አቅርቦት እጥረት ለማቃለል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ተግባር ላይ እንደሚውል አስረድተዋል ።

ከዚህም ከ400 ሺህ ኩንታል በላይ የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ማሽላ፣ጤፍ፣ ሰሊጥና አኩሪ አተር ምርጥ የሰብል ዘር እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

በኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የአየሁ እርሻ ልማት ስራ እስኪያጅ አቶ ማስረሻ እንግዳ እንዳሉት፤ ድርጅቱ በ1 ሺህ 75 ሄክታር መሬት ላይ የዘር ብዜት ስራ ማከናወን ጀምሯል።


በዚህም "ዜድ ኤስ ኤም 721" የተሰኘ የተሻለ አዲስ የበቆሎ ዝርያ በማመቻቸት በ350 ሄክታር መሬት ላይ ዘር እያባዙ መሆኑን አመልክተዋል።

እንዲሁም ድርጅቱ ከአማራ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝና ከኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር ውል በመውሰድ ''ቀቀባ፣ ዳንፌና ኦጎልቾ'' የተሰኙ የስንዴ ዝርያዎችን በ725 ሄክታር መሬት ላይ የዘር ብዜት ለማከናወን የእርሻ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በምርት ዘመኑ በ50 ሄክታር መሬት ላይ "ቢኤች 661" የተሰኘ የበቆሎ ዘር ብዜት እያከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በምዕራብ ጎጃም ዞን በግል ዘር በማባዛት የተሰማሩት አቶ ቢኒያም ሙላት ናቸው።

ባለፈው ዓመት በዘር ከተባዛው መሬት ከ281 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ የሰብል ዘር ተሰብስቦ ለ2017/2018 የምርት ዘመን ልማት ጥቅም ላይ እየዋለ እንደሚገኝም የግብርና ቢሮው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026