የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች ነው- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 30/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባች መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፤ ከ2026 - 2030 የሚተገበረውን ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ይፋ አድርገዋል።

ሁለተኛው የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።


ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ዘርፈ ብዙ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ተጨባጭ የዲጂታል እድገት ማስመዝገቧን ጠቅሰው፤ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት በሚያስደንቅ ፍጥነት መስፋፋቱን ተናግረዋል።

መንግሥት በወሰዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች እና የመሠረተ ልማት ግንባታ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ጠንካራ መሠረት መገንባቱን ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ፋይናንስ ምህዳሩ በየዓመቱ ከ18 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ ግብይቶችን እያስተናገደ ነው ብለዋል።

የዘርፉ ለውጥ ፈጣንና አስተማማኝ የቴሌኮምና የኢንተርኔት ተደራሽነትን በማስፋት የኢኮኖሚውን ዲጂታል ጉዞ እያፋጠነ መሆኑን ገልጸዋል።

የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ያሉ የዲጂታል የመንግሥት አሠራሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ አገልግሎቶችን በአንድ ስፍራ በማሳለጥ እንግልትን እየቀነሱና ግልጽነትን እያሻሻሉ መሆኑን ተናግረዋል።

ብሔራዊ ባንክ አሠራሮችን በማዘመን ለሞባይል ገንዘብ ዝውውር፣ ለክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች እና ለፈጠራ ባለሙያዎች ምቹ ምህዳር መፍጠሩን ተናግረዋል።

በኢት-ስዊች የተደገፈው ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ አሠራር ከፍተኛ ገንዘብ በባንኮች መካከል እና በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ እንዲንቀሳቀስ አስችሏል ነው ያሉት።

የቴሌብር ፈጣን ተደራሽነትና ለአጠቃቀም ምቹ መሆኑ የዕለት ተዕለት የዜጎችን ኑሮ እያሳለጠ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን ጨምሮ ዲጂታል ክህሎትን የማጎልበት ሥራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶች ኢኮኖሚውን ወደ ፊት የሚያሻግሩ ብሔራዊ መሠረተ ልማቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ነገር ግን ከተደራሽነት ባሻገር ትርጉም ባለው አጠቃቀም ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ነው ያሉት።

የዲጂታል አጠቃቀምን ማሳደግ የአርሶና አርብቶ አደሮችን ህይወት በማሻሻል፣ ሥራቸውን በማቅለል፣ የፋይናንስ አገልግሎትን በቀላሉ እንዲያገኙ በማድረግ የአካታች ኢኮኖሚ ዕድገት ይፋጠናል ብለዋል።

የዲጂታል ጉዟችን ቀጣዩ ምዕራፍ ሊለካ የሚገባው የህዝባችንን ህይወት በማሻሻል ረገድ ነው ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።


ከዚህ አኳያ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ መሠረተ ልማትን እንድናጠናክር፣ አጠቃቀምን ማስፋት፣ ክህሎቶችን መገንባት እና ችግሮችን የሚፈታ ፈጠራን የማበረታታት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘመኑን የዋጀው ይህ ስትራቴጂ፣ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና ማህበራዊ ዘርፎች ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የዲጂታል ግብይት ማህበረሰቡን የሳይበር ደህንነትን በማረጋገጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት እና ኃላፊነት በተሞላበት አሠራር ህዝቡን ማገልገል እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በጋራ ዓላማ በማሳተፍ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚሆን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የዲጂታል መፃኢ ዕድሏን የሚወስን ጠንካራ መሠረት አስቀድማ ገንብታለች ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይ ከዲጂታል ተደራሽነት ወደ ተፅዕኖ እና ወደ ጋራ ብልጽግና የሚደረገውን ሽግግር ማፋጠን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026