የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 30/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ።

በክልሉ እስካሁን ከ22ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን አስታውሰው ሰላምን በመግፋት በጥፋታቸው በቀጠሉት ላይ ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ፤ የክልሉን ወቅታዊ የሰላምና የልማት እንቅስቃሴ በማስመልከት ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የክልሉ መንግስት ከለውጡ ወዲህ ከገጠሙት ፈተናዎች መካከል በተወሰኑ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር እንደነበር አስታውሰው በዘላቂነት ለመፍታት ብዙ መሰራቱን አስረድተዋል።

በክልሉ የህግ የበላይነትን ከማስከበር በተጓዳኝ የተሳሳተ መንገድ ላይ የነበሩ አካላት ወደ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ ጥረት ተደርጓል ብለዋል።

ከመንግስት የሰላም ጥሪ ባለፈ በአባ ገዳዎች፣ በሃዳ ሲንቄዎች፣ በሃይማኖት አባቶች እና በሀገር ሽማግሌዎች አማካኝነት ለሰላም ምላሽ እንዲሰጡ መሰራቱን አንስተዋል።

በዚህም መሰረት ከ22 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪን በመቀበል የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለሳቸውን ገልጸዋል።

ከቀድሞ ታጣቂዎቹ መካከል 10ሺህ የሚሆኑት የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን ሌሎች እንደየፍላጎታቸው ወደ መደበኛ ህይወታቸው ተመልሰዋል ብለዋል።

የመስሪያ ቦታ እና 581 ሚሊዮን ብር ብድር ተመቻችቶላቸው ወደ ስራ የገቡ እንዳሉ ገልጸው ወደ ትምህርት እና ወደ መንግስት ስራም የተመለሱ እንዳሉ ጠቅሰዋል።

በክልሉ የህግ የበላይነትን በማስከበር ሁለንተናዊ ልማትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም አረጋግጠዋል።

“በጽንፈኝነት ለጥፋት ዓላማ የተሰለፈ ሁሉ የትኛውንም ቋንቋ ቢናገር ጽንፈኛ ነው” ያሉት አቶ ሃይሉ የኦሮሞም ይሁን የአማራ ጽንፈኛ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ይጠናከራል ብለዋል።

በቅርቡ በሆሮ ጉዱሩ እና ምስራቅ ወለጋ ዞኖች የተወሰኑ አካባቢዎች በጽንፈኞች ላይ ጠንካራ እርምጃ በመወሰዱ በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026