🔇Unmute
ባህር ዳር ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ በሕገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ ንብረትን ለመንግሥትና ለሕዝብ ለማስመለስ የሚያስችለው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ዜጎች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን የእኩል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተመላከተ፡፡
የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ የንብረት ማስመለስ አዋጅን ተግባራዊ በማድረግ የሕግ-የበላይነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት የዳያስፖራው ማህበረሰብ በሀገሩ ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርግበትን ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
በአማራ ክልል በሕገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ ንብረትን ለመንግሥትና ለሕዝብ ለማስመለስ የሚያስችለውን የንብረት ማስመለስ አዋጅ ቁጥር 1364/2017 ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው።
ቢሮው በሕገ-ወጥ መንገድ ንብረት ያካበቱ ግለሰቦች ላይ ተገቢውን ክትትል በማድረግ ማስመለስ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ብርሃኑ ጎሽም እንደገለጹት፣ ይህ አዋጅ ዜጎች በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን የእኩል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው።
አዋጁ ግለሰቦች በሕጋዊ መንገድ ብቻ ሀብት የማፍራት ባህል እንዲያዳብሩ በማድረግ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ይቀንሳል ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ የአዋጁ ትግበራ የዜጎችን የገቢ ልዩነት በማጥበብ ለዘላቂ ሰላምና ደህንነት መሰረት የሚጥል መሆኑን አንስተዋል።
የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው በበኩላቸው፣ አዋጁ በኢኮኖሚ ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመከላከል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

አዋጁ ወንጀለኞችን በእስር ከመቅጣት ባለፈ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ ያካበቱትን ንብረት እንዲመልሱ የሚያስገድድ መሆኑንም አመልክተዋል።
ያለአግባብ የተዘረፈና የተከማቸ ሃብትን ለማስመለስ በሚደረገው ጥረት ጠቅላይ መምሪያው ከፍትህ ቢሮና ሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ይህም የዜጎችን የገቢ ልዩነት በማጥበብና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ የክልሉን ዘላቂ ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ እንደሚያስችልም አመልክተዋል።
የንብረት ማስመለስ አዋጅ በሙስናና በተለያዩ ሕገ-ወጥ ተግባራት የተከማቸ ሀብት ለልማትና ለሕዝብ ጥቅም እንዲውል ለማድረግ መውጣቱ ይታወሳል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026